Pages

Wednesday, 17 April 2013

" ha yalweledew "

" ሀ ያልወለደው"
        ጎደሎ ሃሳቦች---
ተዳግመው ካልታዩ
       ጭብጣቸው ህመም
ከሠው አያዋዩ ---
      ጥበብም አንዲህ ነች
ለባዶ ጠቢብ---
     ጥለት የለሽ ገላ
ሽፋን ነጠብጣብ:::
ዳሩ ግን ይሻላል።
         ይበጃል።
         ያ ጥበበኛ---
በመስማት የኖረ
    የ ታሪ ሙረኛ---
         ደደብ---
     ---ደንቆሮ ጆሮ
    የማይረባ---
 ---መሃይብ ከበሮ
ከ"ሃ " ጥርብ ያልሆነ---
        ከ"ዋ" የቀመረ!
ልቡንና ልቦናውን
       ነጣጥሎ ያልኖረ!
ብዙ ያስተምራል።
ልቆ ያስተውላል።
ጠጋ ብለው ቢያዩት አላውቅምን ያውቃል።

                                           የ ምስራቁ ሠገል (ማሴ )        08/08/2005 ዓም 

1 comment: