Pages

Thursday 23 January 2014

             ** ተወርዋሪ ኮከብ **


                          እንደተለመደው የከተማው ዋና ዋና ጎዳናዎች ያለ እረፍት የእግረኞች ና የተሽከርካሪዎች ወድያ ወዲህ መናወዝ ---እላይ ታች መኳተን ያለ መሰልቸት እያስተናገዱ ነው።እኩለ ቀን ለመባልና ላለመባል በሚያስቸግር ሰዓት ከእጁ የማትጠፋውን ማስታወሻ በግራ እጁ መዳፍ እንደያዘ ታክሲ ውስጥ ሊሰጥሙ ጉጉት ላይ ካሉት በርካቶች ጋር ቆሟል።በአንድ እጁ ፀጉሩን ማፍተልተሉን አልተወም። የተንጨባረረ ፀጉሩ ሲያዩት ብዙም ከተራ አልወጣም። ሰዉ ወደየፊናው ሊሰማራ የለገሃሬ ታክሲዎች መጥፋታቸው---። ከየት መጣ የተባለ ታክስ ፊታቸው ድቅን። ሁሉም ወደሚከፈተው የታክሲው በር በሚሻሙበት ቅፅበት የ እስክንድር ስልኩ ተንጫረረች። ፈጠን ብሎ አነሳው።
                                 " ሀሎ----ይሀው መጣሁ ታክስ አጥቼ ነው---እንደውም ታክሲ መጣ። እዛው ጠብቂኝ---" ከማለቱ የታክሲው ረዳት -----
                                  " ምድነው ግርግሩ---ቆይ እስቲ ---" የሰማው የለም ።
                                  "ቀፊራ ነን  --- መጋላ ---አቦ ኮኔል ያዘን። "
                                   "እኔ አልጭንም እንዴ -----" ረዳቱ።   አጉረመረሙ። ተበሳጩ። ተሳደቡ።

                   --------------------------           -------------------------------------         ---------------------------

                              ፀሐዩ እየበረታ ነው።የዓለም ፋብሪካዎች በ ድሬዳዋ ሰማይ ትይዩ የተተከሉ ይመስል የ ኦዞን ንጣፍ በመቀደዷ ፀሐይ ጨክናለች ያስብላል።  አሁንም ተደወለ ።አነሳው።
                                   " እኮ እየመጣሁ ነው---ግድ የለም አልቆይም ። እሺ---" ፊቱ አጨማተረ ።የንዴት ፍሰት ከውስጡ እንደ አዋሽ ወንዝ እየተገለባበጠ የሃይሉ ብዛት ፊቱ ላይ ይፋ ወጣ። መንገደኛው  እያጉረመረመ  ነው።
                           ሰዓቱ አልጨበጥ እንዳለ ነው። ይሄዳል ---ይነጉዳል--።ሰዓቱ ከሄደ አይቀር እንደአባይ ወንዝ ግንድ ይዞ ባይዞር  እንኳን እሱን ይዞት ቢሄድ ተመኘ። ሙቀቱ አይሏል ።እስክንድር የያዛት ማስታወሻ በራስ ቅሉ ከፍ አድርጎ ፀሐይቱን ለመከላከል ሞከረ።  በሰፈሩ (ለገሃሬ ) የተሽከርካሪ ጩሀት ና የ ሰው ትርምስ ጋብ ብሎ ---ሰዎች በካፍቴርያ በረንዳ ላይ ሻይ ቡና እያሉ ከሰማይ የሚወርደውን አስጠሊታ ገበን ይታዘቡታል።የቆሙ ተሳፋሪዎች ታከታቸው። ተበታተኑ።

                          እስክንድር በአለባበሱ ብዙም አይታማም።በፀሐይ ትኩሳት የተለበለበው ሸራ ጫማው ምን ያህል ረመጥ እንደሆነበት ያስታውቃል።በንፅህናው ይሁን በእድሜው የማያስታውቅ የነተበ ጂንስ ሱሪ አድርጓል።አንገተ ክብና ቀጭን የሆነ ሹራብ ለብሷል። ክስት ባለው ፊቱ ላይ ተቆልምሞ የሚታየው አፍንጫው ዳገት ላይ ግማሽ ፊቱ የጋረደ ጥቁር መነፅር አጥልቋል። ቀስ እያለ ወደ አንድ ፑል ማጫወቻ ቤት ተጠጋ። ገባ። ቆሞ ያያል። ደክሞታል።

 ------------------------------             ------------------------------------                      ---------------------------

                              ሃና ይመጣል ብላ የምትጠብቀውን እስክንድር ቆየባት። ግራ ገባት። 'እየመጣሁ ብሎኝ? ' ትላለች ለራሷ። በድጋሚ ደውለች ----
                                   " ምነው ቀረህ --እየጠበቁህ ነው።" ግንባሯ ላይ የአግድም መስመሮች ንግግሯን ተከትለው ብቅ አሉ።
                                    " ታክሲ አገኘሁ ብለሀኝ? እሺ ፈጠን በል ---?"
ትውውቃቸው ገና የልጅ ዕድሜ ላይ ቢሆንም በተደጋጋሚ እሱን እሱን ማለቷ አልጣመውም ። እንድእህቱ ነው የሚያያት።

                           ፑል መጫወት አይችልም።ግን ሲጫወቱ ማየት በጣም ያስደስተዋል። ቀጠን ያለውን ቁመናው ግድግዳውን አስደግፎ አይኖቹ ከኳሶቹ ጋር ያንከራትታል ።
          " ዳኛ ትሆናለህ? " ለስላሳ ድምፅ ---ከበጋ ሰማይ በላይ የጠራ ቅላፄ --- የትህትና ይሁን የሌላ ብቻ ደስ የሚል አቀራረብ።
           " አይ እኔ መጫወት አልችልም። " ቃላቶቹ እንደ በቆሎ ፍሬ ተፈለፈሉ። ሳቅ አለች ። ተፍለቀለቀች ።
" መጫወት ሳይሆን ሲጫወቱ ማየት ያዝናናኛል ። " ደገመላት ።
"ተው ባክህ -----" ትስቃለች ። ቀይ በተቀለሙ ክብ እንጆሪ መሳይ ከንፈሮቿ መሃል ሐጫ የመሰሉ ጥርሶች የበለጠ አስዋቧት ።
                            "  እዚህ ሰፈር ነህ ? " አጠር ያለች ---ቀይ ፊት ያላት ቆንጆ ነች።
                            " አይ---" ባጭሩ መለሰላት። አትኩሮ አያት---
                            " ሰላም እባላለሁ። " እጇን ስትዘረጋለት እንደ ቁልህ በተስተካከለ ፊቷ ላይ የብርሃን ፀዳል እየፈካ ታየው ---።
                           " እስክንድር " ተሰባስበው ፑል የሚጫወቱ ጎረምሶች መሃል ሆነው ወጋቸውን እየሰለቁ ቆዩ።ቤቱ የሙዚቃ ድምፅ ሞልቶታል።ሙዚቃውን ለመቀየር ተነስታ ሪሞቱን ጫን እያደረገች ትመርጥ ጀመር----  ድንገት ፈገግ አለች ።     " ምነው ወደድከው? "
                              "አው ቴዎድሮስ ታደሰ ነፍሴ ነው። " ማስታወሻ ደብተር የያዘበት እጁ ከደረቱ እየለጠፈ።                   "ማየት ይፈቀዳል ? " አለችው ማስታወሻውን። በእምቢታ መለሰላት።
                              "ምን ያደርግልሃል ---? "
                              "ምንም ማስታወሻ ደብተር ነች ። " አላት። ገና ለገና ልቦናው ለ' ሰላም ' ያለውን ክፍት ቦታ ይሰጥ ዘንድ ይጠይቀዋል። ።አላቅማማም።
                              " እንዴት እስካሁን አላየሁሽም ። በተደጋጋሚ በዚህ እመላለሳለሁ። "
                              እኔ የሂርና ልጅ ነኝ። እዚህ ለስራ መጥቼ ነው። " ብላ ከመጨረሷ ስልኩ ጠራ ።  ማንሳት አልፈለገም።       " አንሳው እንጂ ? "
                                " አይ እንኪ የለም  በይልኝ " ተርበተበተ። በግርምት ተቀበለችው።
                               "ሄ --ሄ --ሎ -"
                               " ማነሽ አንቺ ደግሞ --? "አስጠሊታ የማመናጨቅ ድምፅ ነበር።
                               " ይ--ቅርታ "
                               "የምን ይቅርታ ---እስክንድርስ --? ማነሽ--? " ጮሀች ።
                               " የለም ወጣ ብሏል። እኔ---" ተዘጋ ስልኩ። " ምንድነው እስክንድር ----"
                               "እሷ ተያትና ----ሂርና ነው ያልሽኝ--? " በደንብ ተግባቡ።


*** * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * * *
የእስክንድር ሰፈር ሳብያን ቢሆንም በተደጋጋሚ 'ሠላም'ን ለማግኘት   ወደ ለገሃሬ መሄዱን አልተወም።ሰላም ቀለል ያለች ልጅ ነች ።ቀን ከሷ ካሳለፈ ማታ ደግሞ ሲያነብና ሲፅፍ ያመሻል። ኪነ ጥበብ ይወዳል።በተለይ ግጥምና ሙዚቃ ያሰክሩታል።
                  "  እኛ ሰዎች ቃላት ነን።  ምድር ደግሞ ያልተፃፈበት ወረቀት  ወይም ቃላቶች በትክክል ያልተሰደሩባት ንጣፍ ----ገጣምያን ደግሞ በዚህ ንጣፍ ላይ እንደ ዘበት የተዝረከረኩ የተፈጥሮ ስሜትን ፣ውበትን ና እይታዎችን እየከሸኑ የሚያስውቡ ስጋና አጥንት የለበሱ መላእክት ናቸው። " ይላል እስክንድር።
              ጠዋት ጠባብ ክፍሉ ውስጥ እያነበበ ነበር።የጠዋት ፀሐይ በመስኮት ቀዳዳ አጮልቃ መፅሐፍ መደርደርያው ላይ አብርታለች። ስልኩ ጮሀች (እ ሪ ሪ ሪ ሪ አለች) ። በጣቱ ኮረኮማት። ሰላም ነበረች። አነሳው።

" ደህና ነኝ -ተጠፋፋን ? እሺ እመጣለሁ ---እሁድም ስለሆነ---እሺ-- እሺ-- ቻው። " ፊቱ ፈካ። ቀና ብሎ በጥቅስ ና በሚወዳቸው ጠቢባን ስዕል የተዋበውን የክፍሉ ግድግዳ ላይ አይኑን ጣለ።
               "እውነት ረቂቁን ማግኘት ሳይሆን  ተጨባጩን መኖር ነው። " የምትል ጎላ ያለች ጥቅስ  ታየችው። ተነስቶ ቁርሱን  በልቶ ትንሽ ካረፋፈደ በሁዋላ ወደ ሰላም ከነፈ።

*  * *** *                   ****************                  ***************   *******
ከታክሲ እንደወረደ ወደ ፑል ቤት ሲያመራ ከወትሮ በተለየ በረንዳው የጎረምሶች ዳና ሳይሆን አንዲት ቆንጆ ፀጉሯ ክምክም ጎፈሬ የሆነች ብፅእት-----ቁጭ ብላ ከፊት ለፊቷ ደግሞ የሲኒ መደርደርያ ከነጀበናው አስደማሚ ሕይወት ዘርተውበት ታየው። በፈገግታ ተቀበለችው። በጣም ደስ ብሎታል።
                       "ምነው እንቁጣጣሽ ነው እንዴ ? " እየሳቀ---በአይነ ቂጡ በፍቅር አይን እየገረመማት -----ከቆይታ በሁዋላ ደስ የሚል ጨዋታ እየተጫወቱ በመሃል-----
                      " ለቤተሰቦችሽ ስንተኛ ልጅ ነሽ? " ብሎ ጠየቃት።  ነገረችው ። ቡናው ፈልቶ እየጠጡ ሳለ ጋብ ያለውን የጨዋታቸው ድባብ የናደ ጥያቄ ከወደ እስክንድር-----
                      " ምነው ትክዝ አልሽ----" ወድያው በምሽት ሰማይ ጎልተው የሚታዩ ከዋክብት የመሰሉ አይኖቿ የ እንባ ጠብታ አፍልቀው በብርቱካን መሳይ ጉንጭዋ አረጠቡት ። ደነገጠ ። ሊያረጋጋት ሞከረ።  ቤተሰቧ ላይ የተፈጠረ አንዳች ረመጥ ሳያውቅ ነቅቶ እንደሆነ ጠረጠረ። እውነት ነው ።ቆይታ ሁሉንም አጫወተችው። እጅግ የሚያሳዝን የቤተሰቧ ታሪክ አሳልፋ በእምነት አወራችለት። ለቅሶዋ እንድታቆም ጠየቃት። በሁዋላ ላይ ወደ ቀድሞ ስሜቷ ብትመለስም---እስክንድር ግን በጣም ስሜቱ ተነክቶ ነበር።

                ከተለያዩ በሁዋላ ቤቱ ገብቶ አልጋው ላይ ተገለባበጠ ። አሳዘነችው።  ምሽቱ ገፍቶ 6 ሰዓት ሲሞላ የነገረችውን ሁሉ ለመፃፍ ተነሳ። አደረገውም ። ከ 3 ቀን በሁዋላ ደውላ ጠራችው። ሄደ።
                       " እዚህ አልቆይም---ቤተሰቦቼ ጋ ልሄድ ነው ። አንተን መተዋወቄ  ደስ ብሎኛል። እንዳትረሳኝ ። ሰውነቱ ተዝለፈለፈ ። መቀበል አቃተው። ግና ግድ ነው። ከዝያ ቀን በሁዋላ ሠላምና እስክንድር በአካል ተለያዩ  በመንፈስ ግን--------
        ሰላም ማለት ለ እስክንድር በጠዋቱ ጊዜ እንደጤዛ አብራው የነበረች ግና የቀትር ፀሐይ መቋቋቋም ተስኗት ልቡ ውስጥ የቀረች ምልክት ናት።


                                      ተፈፀመ               በ ናሙስ ናኒ             14/05/2006
                                  

Tuesday 21 January 2014

from stumble


8 Great Philosophical Questions That We'll Never Solve

8 Great Philosophical Questions That We'll Never Solve
Philosophy goes where hard science can't, or won't. Philosophers have a license to speculate about everything from metaphysics to morality, and this means they can shed light on some of the basic questions of existence. The bad news? These are questions that may always lay just beyond the limits of our comprehension.
Here are eight mysteries of philosophy that we'll probably never resolve.

1. Why is there something rather than nothing?

8 Great Philosophical Questions That We'll Never SolveExpand
Our presence in the universe is something too bizarre for words. The mundaneness of our daily lives cause us take our existence for granted — but every once in awhile we're cajoled out of that complacency and enter into a profound state of existential awareness, and we ask: Why is there all this stuff in the universe, and why is it governed by such exquisitely precise laws? And why should anything exist at all? We inhabit a universe with such things as spiral galaxies, the aurora borealis, and SpongeBob Squarepants. And as Sean Carroll notes, "Nothing about modern physics explains why we have these laws rather than some totally different laws, although physicists sometimes talk that way — a mistake they might be able to avoid if they took philosophers more seriously." And as for the philosophers, the best that they can come up with is the anthropic principle — the notion that our particular universe appears the way it does by virtue of our presence as observers within it — a suggestion that has an uncomfortably tautological ring to it.

2. Is our universe real?

8 Great Philosophical Questions That We'll Never SolveExpand
This the classic Cartesian question. It essentially asks, how do we know that what we see around us is the real deal, and not some grand illusion perpetuated by an unseen force (who René Descartes referred to as the hypothesized ‘evil demon')? More recently, the question has been reframed as the "brain in a vat" problem, or the Simulation Argument. And it could very well be that we're the products of an elaborate simulation. A deeper question to ask, therefore, is whether the civilization running the simulation is also in a simulation — a kind of supercomputer regression (or simulationception). Moreover, we may not be who we think we are. Assuming that the people running the simulation are also taking part in it, our true identities may be temporarily suppressed, to heighten the realness of the experience. This philosophical conundrum also forces us to re-evaluate what we mean by "real." Modal realists argue that if the universe around us seems rational (as opposed to it being dreamy, incoherent, or lawless), then we have no choice but to declare it as being real and genuine. Or maybe, as Cipher said after eating a piece of "simulated" steak in The Matrix, "Ignorance is bliss."

3. Do we have free will?

8 Great Philosophical Questions That We'll Never Solve
Also called the dilemma of determinism, we do not know if our actions are controlled by a causal chain of preceding events (or by some other external influence), or if we're truly free agents making decisions of our own volition. Philosophers (and now some scientists) have been debating this for millennia, and with no apparent end in sight. If our decision making is influenced by an endless chain of causality, then determinism is true and we don't have free will. But if the opposite is true, what's called indeterminism, then our actions must be random — what some argue is still not free will. Conversely, libertarians (no, not political libertarians, those are other people), make the case for compatibilism — the idea that free will is logically compatible with deterministic views of the universe. Compounding the problem are advances in neuroscience showing that our brains make decisions before we're even conscious of them. But if we don't have free will, then why did we evolve consciousness instead of zombie-minds? Quantum mechanics makes this problem even more complicated by suggesting that we live in a universe of probability, and that determinism of any sort is impossible. And as Linas Vepstas has said, "Consciousness seems to be intimately and inescapably tied to the perception of the passage of time, and indeed, the idea that the past is fixed and perfectly deterministic, and that the future is unknowable. This fits well, because if the future were predetermined, then there'd be no free will, and no point in the participation of the passage of time."

4. Does God exist?

8 Great Philosophical Questions That We'll Never SolveExpand
Simply put, we cannot know if God exists or not. Both the atheists and believers are wrong in their proclamations, and the agnostics are right. True agnostics are simply being Cartesian about it, recognizing the epistemological issues involved and the limitations of human inquiry. We do not know enough about the inner workings of the universe to make any sort of grand claim about the nature of reality and whether or not a Prime Mover exists somewhere in the background. Many people defer to naturalism — the suggestion that the universe runs according to autonomous processes — but that doesn't preclude the existence of a grand designer who set the whole thing in motion (what's called deism). And as mentioned earlier, we may live in a simulation where the hacker gods control all the variables. Or perhaps the gnostics are right and powerful beings exist in some deeper reality that we're unaware of. These aren't necessarily the omniscient, omnipotent gods of the Abrahamic traditions — but they're (hypothetically) powerful beings nonetheless. Again, these aren't scientific questions per se — they're more Platonic thought experiments that force us to confront the limits of human experience and inquiry.

5. Is there life after death?

8 Great Philosophical Questions That We'll Never SolveExpand
Before everyone gets excited, this is not a suggestion that we'll all end up strumming harps on some fluffy white cloud, or find ourselves shoveling coal in the depths of Hell for eternity. Because we cannot ask the dead if there's anything on the other side, we're left guessing as to what happens next. Materialists assume that there's no life after death, but it's just that — an assumption that cannot necessarily be proven. Looking closer at the machinations of the universe (or multiverse), whether it be through a classical Newtonian/Einsteinian lens, or through the spooky filter of quantum mechanics, there's no reason to believe that we only have one shot at this thing called life. It's a question of metaphysics and the possibility that the cosmos (what Carl Sagan described as "all that is or ever was or ever will be") cycles and percolates in such a way that lives are infinitely recycled. Hans Moravec put it best when, speaking in relation to the quantum Many Worlds Interpretation, said that non-observance of the universe is impossible; we must always find ourselves alive and observing the universe in some form or another. This is highly speculative stuff, but like the God problem, is one that science cannot yet tackle, leaving it to the philosophers.

6. Can you really experience anything objectively?

8 Great Philosophical Questions That We'll Never SolveExpand
There's a difference between understanding the world objectively (or at least trying to, anyway) and experiencing it through an exclusively objective framework. This is essentially the problem of qualia — the notion that our surroundings can only be observed through the filter of our senses and the cogitations of our minds. Everything you know, everything you've touched, seen, and smelled, has been filtered through any number of physiological and cognitive processes. Subsequently, your subjective experience of the world is unique. In the classic example, the subjective appreciation of the color red may vary from person to person. The only way you could possibly know is if you were to somehow observe the universe from the "conscious lens" of another person in a sort of Being John Malkovich kind of way — not anything we're likely going to be able to accomplish at any stage of our scientific or technological development. Another way of saying all this is that the universe can only be observed through a brain (or potentially a machine mind), and by virtue of that, can only be interpreted subjectively. But given that the universe appears to be coherent and (somewhat) knowable, should we continue to assume that its true objective quality can never be observed or known? It's worth noting that much of Buddhist philosophy is predicated on this fundamental limitation (what they call emptiness), and a complete antithesis to Plato's idealism.

7. What is the best moral system?

8 Great Philosophical Questions That We'll Never Solve
Essentially, we'll never truly be able to distinguish between "right" and "wrong" actions. At any given time in history, however, philosophers, theologians, and politicians will claim to have discovered the best way to evaluate human actions and establish the most righteous code of conduct. But it's never that easy. Life is far too messy and complicated for there to be anything like a universal morality or an absolutist ethics. The Golden Rule is great (the idea that you should treat others as you would like them to treat you), but it disregards moral autonomy and leaves no room for the imposition of justice (such as jailing criminals), and can even be used to justify oppression (Immanuel Kant was among its most staunchest critics). Moreover, it's a highly simplified rule of thumb that doesn't provision for more complex scenarios. For example, should the few be spared to save the many? Who has more moral worth: a human baby or a full-grown great ape? And as neuroscientists have shown, morality is not only a culturally-ingrained thing, it's also a part of our psychologies (the Trolly Problem is the best demonstration of this). At best, we can only say that morality is normative, while acknowledging that our sense of right and wrong will change over time.

8. What are numbers?

8 Great Philosophical Questions That We'll Never SolveExpand
We use numbers every day, but taking a step back, what are they, really — and why do they do such a damn good job of helping us explain the universe (such as Newtonian laws)? Mathematical structures can consist of numbers, sets, groups, and points — but are they real objects, or do they simply describe relationships that necessarily exist in all structures? Plato argued that numbers were real (it doesn't matter that you can't "see" them), but formalists insisted that they were merely formal systems (well-defined constructions of abstract thought based on math). This is essentially an ontological problem, where we're left baffled about the true nature of the universe and which aspects of it are human constructs and which are truly tangible.

Saturday 18 January 2014

                                        ለምን ይፍረስ ?
                   (አጭር ታሪክ) ምናባዊ           በ ናሙስ ናን

ተሸፋፍኜ አንደተኛሁ ነበር ከውጭ የሚጠራኝ ሰው አንዳለ የተረዳሁት።አህቴ ነበረች።ያው "ቁርስ ደርሷል" ልትለኝ ነው።የአየሩ መቀዝቀዝ ተከትሎ አጆቼ ጉልበቴን የሙጥኝ አቅፈው---አይኖቼ ብርድልብስ  ዉስጥ ሌባና ፖሊስ ይጫወቱ ይመስል---ተጨናንቆ  ባደረው አአምሮዬ የተቦኩ የሃሳብ ድሪቶች አያሰሱ ይሆናል።ከ 6 ዓመት በሁውላ ነው ቤተሰቦቼን የተገናኘሁት።ከትላንት በስትያ  አንደመጣሁ ሰፈሩ ብዙ ተቀይሮ አላገኘሁትም።አንደመጣሁ ተከርችሞ የሰነበተው የ አቢ ተማም ያረጀች ጎጆ ላይ ነበር ቀልቤ ያረፈው።የአርሳቸው ቤት ከኛ ቤት ቀጥሎ ነው ያለው።

----------------------------------------------------------------------------------------------  ---------  ----- -----------------
የተኛሁበት ክፍል በጣም ጠባብ ነች።ያኔ ከሰፈር ከመራቄ  በፊት አዚህ ነበር የማርፈው።አዳር የለበስኩት አንሶላ ገፈፍ አድርጌ አይኔ ግድግዳው ላይ አሳረፍኩ። 3 በሸራ የተሰሩ ስአሎች ፈገግታ ርቋቸው --- የፀሐይ ብርሃን ተርበው ---አጅግ ወይበው ይታዩኛል።የ አቢ ተማም አጅ የ ስነ-ስዕል ዓይን የሚኳልበት ድንቅ አጅ ነበር።ዉስጤ ጭንቀት ሞላኝ።አአምሮዬ ሰላም አጣ።አይኖቼ አንባ አረገዙ።ቁጭት---ቁጭት---"ባይሆንስ" የሚል  የሃሳብ ፍጭት ከራሴ ገጠምኩ።አውቄ ቁርስ ላለመብላት አረፋፈድኩ።ሆኖም መተኛቱ አልወደድኩትም።አዚህ ተኝቼ ምንም አልሰራም።ስለዚህ ወደ ዉጭ መውጣት አለብኝ።ወጥቼ የቅያስ መንገዱን ተከትዬ ዋናውን አስፋልት አንደወጣሁ ዉስጠቴ ወደ አገና -ማዞርያ መታጠፍ አንዳለብኝ ይነግረኛል።መሄድ ጀመርኩ።----ደረስኩ።አስፋልቱ በሰው ትርምስ ሰላሙን አንዳጣ ያስታውቅበታል። ከሰማይ አሞሮች ያንዣብባሉ። አይነ መሬት ላይ ከቀረው የአሞሮቹ ምስል አያንከራተትኩ ---'አሞራ ብሆንስ?' የሚል የዉስጥ ሃሳቤ ለአቅመ-ንግግር ሳይደርስ ቀርቶ ዋጥኩት።ብሆን ግን ከላይ ወደታች ሳይ አስፋልቱ አንድ አጁ ያጣ 'ተ' ፊደል ቅርፅ ሳይኖረው አይቀርም ብዬ አስብኩ።

                                "ሰሚር"--------ከሃሳቤ መንጭቆ ያወጣኝ ጥሪ።አበራ ከበስተኋላዬ አየተከተለኝ ኖሯል።ባልሰማ አይነት ዝም አላልኩትም።ተገናኝን።አየተንሰፈሰፈ አናገረኝ።የድሮ ወዳጄ ።ብዙ አንደተቻወትን---------
                         " አረስቼው --ከቤት ጥራው ተብዬ ነው የተከተልኩህ---ግን አንተ አንዴት ነህ?"
ጥሩ ስሜት ላይ ስላልነበርኩ ልሂድ አልሂድ አያልኩ ጥቂት ተወዛገብኩ።
                             "ለምን ፈለጉኝ?"   አልኩት።
                             
                             "የ አቢ ተማም ቤት ሊፈርስ መሰለኝ ----"  አንገቱን ደፍቶ።
                             "ለምን?" ጮህኩበት አሱ ያፈረሰው መሰለብኝ።
                             "አኔ'ጃ "
'ድንቄም  ማፍረስ' ----በሃሳቤ-- በፍጥነት ቤት ሄድኩ።
ብዙ ሰው ተሰብስቧል።ያወራሉ።ይተነብያሉ።ብዙ ብዙ-----

                                         "ማን ተጠግቶ ነው የሚነካው?"
                                         "ስንት ዓመት የተዘጋ ቤት---የ አጋንንት መናሀርያ።"
                                          "ቢቀርስ ----የጠንቅዋይ ቤት ከመነካካት ኤድያ ---"
                                          
                                         "ልጁ መጣ መሰለኝ አሱ አንደሆነ ከሽማግለው በምን ተሽሎ--"
የሚያወሩት ይዘገንናል። አያዳምጡም ።
---------------------     -------------    -----------------   ------------- -----------   --------------     -------------

የኔ መምጣት የፈለጉት ለሌላ አይደለም።ቤቱን ከፍቼ።ውስጥ ያለውን አይተው ለማፍረስ---። 'አቢ ተማም' አባቴ ይሁኑ አያቴ ----ዘመድ ይሁኑ ባዳ የማውቀው ነገር የለም። በሕይወት አያሉ ከሳቸው አሳልፍ ነበር። በዚህ የተነሳ ከአባቴ ብዙ ችግር ውስጥ ገብቻለሁ።ታታሪ ነበሩ።ጥበብ አፍቃሪ።ሩህሩህ--ቸርና ለጋስ አረጋዊ።ይህን ሁል ግን በሕይወት በነበሩ ሰዓት ያወቀው አልነበረም።ፈረንጅ መጥቶ ስለርሳቸው ስላልፃፈ ይሆናል---ወይም --? ሁሌም በመጥፎ ስም ሲጠሩ ኖሩ ጥበብን ባወቁ።ተሰደቡ።

----------------------------      -------------------------     ----------------------    ---------------- ----------------------
አንድ ቀን ብዙ አጫወቱኝ።ስለ ጠልሰም አውቀት እንኳን ሰምቸው በምናብ የማላስበውን ቁምነገር አወጉኝ።

"ይህ ጥበብ በ ዘር የሚተላለፍ አንጂ አንዲሁ የሚለቀም የሽንብራ ፍሬ አይደለም" ይሉኝ ነበር።የዚህ ጥበብ ኃይል አጅግ ብዙ ሚስጥራቶች ያዘለ  መሆኑ ጭምር።ለበሽታ ፈውስ የሚሆኑ ጥበቦችን የተለያዩ አፅዋቶችን በመቀመም ማግኘት አንደሚቻልና ---የሚሰውር አፅ ሁሉ አንዳላቸው ነገሩኝ።ተገረምኩ።
 
         በርካቶች  አንደአንሽላሊት በጨለማ  አየመጡ ፈወስ ጠይቀው አግኝተዋል።---"ባጎረስኩ ---" አንዲሉ ስነጋላቸው ግን ጠንቅዋይ ፣ደጋሚ አያሉ መቀመጫ አንዳሳጧቸውም ተረኩልኝ። ምን አንደሚያጣቅሱበት የማላውቀውን መፅሃፋቸው በተለያዩ ቀለማት ተዥጎርጉሮ ሕቡአ ፊደላት ፣ስአሎች ተስለውበት አይ ነበር። የ ብዙ ሚስጥራት ቁልፍ አንደሆነም ሳይነግሩኝ አላለፉም።የበለጠ በቀርብከዋቸው ቁጥር ብዙ ወደዱኝ።የ ጠልሰምን አውቀት ልያወርሱኝና ያለተረካቢ ሜዳ አንዳይቀር አንደሚያስተምሩኝ ቃል ገቡልኝ።አደረጉትም። አባቴ-------

                  "የዚህ ጠንቅዋይ በት መሄዱን ካልተውክ ቤት አንዳትገባ።"  ሲል ፎከር።የጥበብ ጣአም ገና በጠዋቱ ያጠጣሁት ልቤ የአባቴን ዛቻ ቦታ አልሰጠውም።  አየቆየ ግን -----


ፊታቸው መገርጣት ሲጀምር (በሽምግልና)፣አጆቻቸው ለብሩሽ አንክዋን ሲሰንፉ ሳይ ሳግ ይተናነቀኝ ነበር።

አንድ ቀን ላንጫ ኮረብታ ለመድኃኒት ቅመማ በሄዱበት ከዛፍ ላይ ወድቀው ሕይወታቸው ማለፉን ያወቅኩት ልፈልጋቸው ስሄድ ነበር።አንደዝያ ቀን አዝኜ እንኳን እንኳን አላውቅም።ከቀብራቸው በሁዋላ ሰው ሁሉ አኔ አንዳስገደልክዋቸው ያስብ ነበር።የመንደሩን ወሬ አላስቀምጥ ሲለኝ ጥቂት መፅሃፎቻቸው ይዤ አዲስ አበባ ገባሁ።ለ 6 ዓመታት ከብዙ ሰው ጋር ስተዋወቅ የጠልሰም አውቀት ጨምሮ የሀገሬ ሕዝብ የዘነጋቸው በርካታ ጥበቦች አንዳሉ ተረዳሁ።
           ዛሬ ከ 6 ዓመታት በሁዋላ ------------
ለዓመታት ጥበብ የታጨቀበት በት  ለማፍረስ ለተሰበሰበው ሰው አይኑ አንዲገለጥ ፈልግኩ ። ብዙ ለፍቼ አሳመንኩአቸው። በግልፅ ባይቃወሙትም  "ቤቱ አይፍረስ" የሚለውን ሃሳብ በውስጣቸው የጠሉ አይጠፉም።አኔም ከዘመናዊው የሕክምና ጥበብ አቆራኝቼ የርሳቸውን ፈለግ ለማስቀጠል ቃል ገባሁ። ቤቱም ታደሰ። ጥበብም ነገሠ ።ሁሌም አሸናፊ ነውና።

                                   (ናሙስ ናኒ ) 10/05/2006

Sunday 12 January 2014

Thursday 2 January 2014

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመብት ንቅናቄና የኢትዮጵያ መንግሥት፤ ተመቻማች ወይስ ተገዳዳሪ?

ጃዋር ሙሐመድ
(Translated by Isaac Eshetu)
በኢትዮጵያ መንግሥትና በሙስሊም የመብት ንቅናቄ መሪዎች መካከል የተፈጠረውን ፍጥጫ ለመተንተን ብዙ ተሞክሯል። የንቅናቄ አራማጆቹ መንግሥት ከውጭ ያመጣውን የሃይማኖት ቀኖና በግድ በመጫን በሃይማኖታቸው ጣልቃ እየገባ እንደሆነ እየተናገሩ ነው። መንግሥት ደግሞ በበኩሉ የፍጥጫው ምንጭ ‹‹አክራሪነት›› እና ከአገሪቱ ውጭ ያሉ አካላት እጅ እንደሆነ እየገለጸ ሲሆን ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሃይማኖትን ለፖለቲካዊ ጥቅማቸው እያዋሉት እንደሆነ እየተናገረ ነው። ተቃዋሚዎች ደግሞ በተቃራኒው መንግሥት ሃይማኖትን ለ‹‹ከፋፍለህ ግዛ›› መርሁ እያዋለው እንደሆነ ይናገራሉ።‹‹የትኛው ትክክል ነው?›› ነው የሚለውን ልተወውና ሌላ የበለጠ አንገብጋቢ ጥያቄ ላንሳ… ‹‹የውስጥም የውጪም የፖለቲካ ሥራ ፈጣሪዎች (political entreprenuers) ከስትራቴጂያዊ ዓላማቸው ፍሬም ሥር ቀርፀው ለመጠቀም እየተሻሙበት ያለው የሙስሊሙ ኅብረተሰብ እያደገ የመጣ ፖለቲካዊ ንቃት እና ንቅናቄ እንዴት ሊከሰት ቻለ?
ክስተቱን ሊያብራሩ የሚችሉት ምክንያቶች ዐራት ናቸው። አንደኛ፡- በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ዘንድ እየተፈጠሩ የነበሩት ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ለውጦች የተሻለ ተሳትፎና ፖለቲካዊ ውክልናን የግድ የሚፈልጉ መሆናቸው። ሁለተኛ፡- ባለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት ኢስላማዊ መነቃቃት (revivilism) በከፍተኛ ሁኔታ በማደጉ። ሦስተኛ፡- መንግሥት እኒህን ለውጦች ለማስተናገድ የሚችል ከባቢ በድርጅታዊ መዋቅሮቹና ከሕዝቡ ጋር በሚያገናኙት መዋቅሮች ባለመፍጠሩ። ዐራተኛ፡- የመንግሥት ፖሊሲዎችና ታክቲካዊ አካሄዶች የኢስላማዊ ተቋማትን ነጻነት ያዳከሙ በመሆናቸው፤ በዚህም ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ቅያሜ ውስጥ በመግባቱ።የእነዚህ ዐራት ዋነኛ ምክንያቶች የእርስ በርስ መሥተጋብር ሰፊ ሃይማኖታዊ መነቃቃትና ፖለቲካዊ ንቃተ-ሕሊናን ፈጥሯል። እስቲ ዐራቱንም ምክንያቶች ሰፋ አድርጌ ለመተንተን ልሞክር።
1. 1. ሙስሊሙበኢትዮ
ጵያፖለቲካውስጥየነበረውዝቅተኛተሳትፎናውክልና
በቀደመው ታሪክ እስልምና በፖለቲካና በሃይማኖት ጭቆና ሥር ሲያልፍ የቆየ ቢሆንም እንደ አስተሳሰብ ወይም ማንነት ሆኖ ለፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማደራጃነት (mobilization) የዋለበት ጊዜ እምብዛም አልነበረም ማለት ይቻላል። በሌላ አነጋገር ሙስሊሞች በኢትዮጵያ ፖለቲካ የነበራቸው ተሳትፎ ዝቅተኛ ነበር እንደማለት ነው። ሙስሊሞች ዛሬም እንኳ የኢትዮጵያ ሕዝብ ግማሽ ያህል ቢሆኑም በፖለቲካ ልሂቃኑ መካከል ያላቸው ውክልና እጅግ ዝቅተኛ ነው። ለዚህ ምክንያት የሆኑ ሦስት ነገሮች አሉ፡-
ሀ/ ከአሥራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን ጀም
ሮ ዋነኛ የፖለቲካ አሰላለፍ ማዕከል የነበረው ሃይማኖታዊ ማንነት በዘውጌ ብሔርተኝነት ተተካ። በክርስትያን መንግሥታትና በሙስሊም ሡልጣኔቶች መካከል የተደረገው ከፍተኛ ፍልሚያ ካከተመ በኋላ በክርስትያኑ መንግሥት እምብርት ላይ የኦሮሞ ሕዝብ መነሣት ግጭቱን ከሃይማኖታዊ ማንነት ይልቅ ብሄርተኝነት ላይ እንዲመሠረት አድርጎታል። በሁለተኛነት ደግሞ እስልምና ቀስ በቀስና ሰላማዊ በሆነ መልኩ በአብዛኞቹ የአገሪቱ ክፍሎች ከተስፋፋ በኋላ ቀድመው ከነበሩበት ባህሎችና ተቋሞች ጋር በመዋሃዱ ገኖ የወጣ ማንነት ከመሆን ይልቅ የባህሉ አንድ አካል እንዲሆን አድርጎታል። በሦስተኛ ደረጃ የዘውዳዊውን ሥርዓት ለማስፋፋት ወደደቡብ የተደረጉት የማዕከላዊ መንግሥት ወረራዎች ወደ መጨረሻ አካባቢ ሃይማኖትን በግድ የማስለወጥ ባሕሪያቸውን መቀየራቸውም ከሃይማኖታዊ ማንነት ይልቅ ብሔርተኝነት ላይ ያተኮረ ቅየራ (assimilation) እንዲጠቀሙ አድርጓቸዋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ራስን የመከላከሉ ትግልም አደረጃጀቱን ከሃይማኖታዊ ማንነት ወደ ብሔር ማንነት ቀይሯል። አጼዎቹ ኃይላቸውን አንድ አድርገው ለማጠናከርና የግቦቻቸውንም ተገቢነት ለማሳመን ቤተ ክርስትያንን የተጠቀሙ ቢሆንም እስልምና የተወራሪ ብሔሮችንም ሆነ ክልላዊ ቡድኖችን የሚያስተሳስር መሆኑ የብሔሮቹን አንድነት ለመጠበቅ ሲባል ለሃይማኖታዊ ልዩነት የሚሰጠው ትኩረት ቀንሷል። በመሆኑም ሃይማኖትን በተመለከተ ብቻ የሚፈጸሙ ጭቆናዎች ራሳቸው የትግል ፉካቸው ብሔርተኛ አደረጃጀት እየሆነ በመምጣቱ ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ ንቅናቄ ሊፈጠር የሚችልበት ዕድል እየጠበበ መጥቷል።
ለ/ ሙስሊሙ በዋነኝነት ተሠማርቶባቸው የነበሩት ሞያዎች፣ በተለይ ደግሞ ንግድና አርብቶ አደርነት ከማዕከላዊው መንግሥት ጋር የሚያጋጩ አልነበሩም። በገጠራማ አካባቢዎችና በሰሜን ሙስሊሞች በጥቅሉ በንግድ ሥራ ነበር የሚሠማሩት። ንግድ ደግሞ ፖለቲከኞቹ እና መሳፍንቱ የማይመርጡት የተገፋ ሥራ ስለነበር ሙስሊሙ ያለተፎካካሪ ዘርፉን እንዲቆጣጠረው ሆኗል። በሌላ አነጋገር ንግድ ለሙስሊሞች ተስቦ ወደላይ ለመውጣት ቀለል ያለ አማራጭ የነበረ በመሆኑ ማንነቱን ከሌላ ሃይማኖት ጋር ካስተሳሰረው መንግሥት ሥር ፖለቲካዊ ተሳትፎ የማድረጉን አስፈልጎት አስወግዶታል።

በተመሳሳይ ሁኔታ አርብቶ አደርነት ከመንግሥት የሥልጣን ማዕከል ርቆ የሚሠራ ሥራ በመሆኑ መንግሥት ቀጥተኛ ቁጥጥር ሊያደርግ የሚችልበት ዕድል አልነበረም። በልዋጩ ትናንሽ አካባቢያዊ መሪዎችን ነጻነት በመሥጠት በፍቃደኝነት እንዲገብሩ ማድረግ ብቸኛው አማራጭ ነበር። ይህ በወረሩት ቦታ ላይ ሠፍሮ በቀጥታ የተፈጥሮ ሐብቱ ለማዕከላዊ መንግሥት እንዲውል ይደረግ የነበረበት አሠራር የሚፈጥራቸው ግጭቶችና ሰበቃዎች እንዳይፈጠሩ ማድረጉ አይቀሬ ነው። በጥቅሉ በዘውዳዊው አገዛዝ ውስጥ ሙስሊም ልሂቃን በፖለቲካ ውስጥ ለመሳተፍ ግፊት አላደረጉም፤ ቢያደርጉም የሚያስተናግድ ሁኔታ (ከባቢ) አልነበረም። በጊዜ ሂደትም ውጤቱ ነጋዴዎች የትምህርትን አስፈላጊነት እንዳያውቁ፣ አርብቶ አደሮች ደግሞ ለመማር ዕድሉን እንዳያገኙ ሆነ።
ሐ/ በሃያኛው ክፍለ ዘመን የመጨረሻ አጋማሽ እያደገ የመጣ ጭቆና እና አመቺ ውጫዊ ሁኔታዎች ቢኖሩም የተራማጅ (progressive) እና ብሔርተኛ (nationalist) የፖለቲካ ዝንባሌ አገሪቱን በመቆጣጠሩ ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ አደረጃጀት (ንቅናቄ) መግቢያ አላገኘም። በግራ ዘመሞች ትግል ሊሳካ የበቃው የሃይማኖትና መንግሥት መለያየትም የሙስሊሞችን ዋነኛ የቅሬታ ምንጭ አስወገደው። የሙስሊሙን ጥያቄ እውቅና በመስጠትና በመደገፍ ተራማጁ የፖለቲካ ዝንባሌ ለብቻው የቆመ ሃይማኖታዊ ትግል እንዳያስፈልግ አደረገ። በተመሣሣይ ሁኔታ ብሔርተኛ (nationalist) እንቅስቃሴዎች (የኦሮሞ፣ ኤርትራና ትግራይ) በሚያደርጉት ትግል የተለያዩ ሃይማኖቶች ተከታይ አባላት ያሏቸው በመሆኑ የሃይማኖት መቻቻልና የባህል ተመሳስሎሽን በመስበክ ሃይማኖትና መንግሥት እንዳይገናኙ ጥረት አድርገዋል። በሌላ አነጋገር ብሔርተኛ ንቅናቄዎች ለሙስሊሞች ሃይማኖታዊ ማንነት፣ ቅሬታና ስሜት እውቅና በመስጠት መሉ በሙሉ ዓላማዊ በሆነው ትግል ውስጥ ግባቸውን እንዲቀርፁ ዕድል ሰጧቸው።
በጥቅሉ የእስልምና ንቅናቄ ወደ ብሄርተኛ ንቅናቄ እንዲለወጥ መደረጉና የሃይማኖት ጭቆና በተራማጅነት እና ብሔርተኝነት በመተካቱ የሙስሊሞች የትግል አሰላለፍ ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ እንዳይሆን አድርጎታል።
1. 2. የሙስሊሙማኅበረሰብመለወጥ
ባለፉት ጥቂት አሥርት ዓመታት የተከሰቱት ማኅበረ-ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ለውጦች ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ቀስ በቀስ ለውጠውታል። የተወሰኑትን እንዳስሳቸው፡-
ሀ/ ንግድ ዛሬ የሙስሊሞች ብቻ ሞያ መሆኑ ቀርቷል። ከ 1967ቱ አዲስ የመሬት ድልድል በኋላ የቀድሞ ባላባቶች እና መሳፍንቶች ወደ ንግድ በመግባታቸው ዘርፉን ተፎካካሪ ያለበት ሙያ አድርጎታል። ከደርግ ውድቀት መልስ ትጥቅ የፈቱ የትግራይ ወታደሮችም የጅማሮ ካፒታል ተወጥቷቸው ወደ ንግዱ መቀላቀላቸው ለገበያው ተጨማሪ ጫና ሆኗል። በፓርቲ የሚተዳደሩ ግዙፍ የንግድ ድርጅቶች መቋቋማቸውና አዋጭ የሚባሉትን ዘርፎች መቆጣጠራቸውም ሙስሊሙ ተሠማርቶባቸው በነበሩት እንደቡና ንግድ ያሉ ዘርፎች ትናንሽ እና መካከለኛ ነጋዴዎች ላይ ጫና ፈጥሯል። እናም ንግድ ለአዲሱ ሙስሊም ትውልድ አዋጭ ሥራ ሊሆን አልቻለም።
የአየር ንብረት ለውጥ በበኩሉ አርብቶ አደርነትን እጅግ አስቸጋሪ ሞያ አድርጎታል። ተደጋጋሚ ድርቅ ከብቶችን እየጨረሰ በመሆኑ የጥንት ሞያቸውን እንዲተዉት እያደረገ ነው። እናም አዲሱ ሙስሊም ትውልድ የአባቶቹን አርብቶ አደርነት ሞያ እየተወ የተሻለ ሥራና ዕድገት እንዲፈልግ አስገዳጅ ሆኖበታል። በአገሪቱ ከሚገኙ የደመወዝ አስገኚ ሥራዎች 80 በመቶው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በመሆናቸው የመንግሥት ሥራ ተቀጣሪነት የተሻለው አማራጭ ሆኗል። ለዘመናዊው የመንግሥት ሥራ ደግሞ ትምህርት የግድ በመሆኑ ሙስሊም ወላጆች ልጆቻቸውን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ወደ ትምህርት ቤት መላክ ጀመሩ። እነዚህ በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ደግሞ ሲመረቁ መንግሥት ሥራ ላይ እንዲመድባቸው መጠየቃቸውና መጠበቃቸው አልቀረም። መንግሥት በበኩሉ ይህንን ጥያቄ ለመመለስ አለመቻሉ አሁን የምናየውን የሙስሊም ማኅበረሰብ የመብት ንቅናቄ (activism) ፈጥሯል።
ለ/ ባለፉት ጥቂት አሥርት ዓመታት ልክ እንደተቀረው የዓለም ክፍል ሁሉ በኢትዮጵያም እስላማዊ መነቃቃት ተከስቷል። መነቃቃት ሲባል የመንፈሳዊነት ፍላጎት መጨመርና የሃይማኖታዊ አስተምህሮቶች መጎልበት ለማለት ነው። ይህ መነቃቃት በተለይ ደግሞ ባለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት በጣም አድጎ ታይቷል። ሃይማኖትን የማጥላላት ዘመቻ ከፍቶ የነበረው ደርግ ማኅበረሰቡን በጥብቅ ማዕከላዊ ቁጥጥር ሸብቦ ለአሥራ ሰባት ዓመታት በማቆየቱ በ 1983 የተከሰተው የከፊል ዴሞክራሲ እና ያልተማከለ (decentralized) አመራር ለውጥ የሃይማኖት አስፈልጎትም ሆነ አቅርቦት እንዲጨምር አድርጓል። የፕሬስ ነጻነት በተነፃፃሪ መልኩ እፎይታ በማስገኘቱም ሃይማኖት ነክ ሥራዎች እንዲተረጎሙ፣ እንዲታተሙና እንዲከፋፈሉ በር ከፍቷል። የመሃይምነት መጠን መቀነስ በበኩሉ ሰዎች ለገበያ የቀረቡትን መጽሐፍት እንዲያነቡ አድርጓቸዋል።
የትራንስፖርት መሠረተ ልማት መዳበር፣ የቴሌ ኮሚውኒኬሽን አገልግሎት መሻሻል፣ እየጨመረ የመጣው ከገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች መርከስ እና በቅርቡ ደግሞ የማኅበራዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ሚዲያዎች መጎልበት የመረጃ ልውውጡን በእጅጉ ጨምሮታል። እኒህ ሁሉ ተዳምረው ሰፊ ሃይማኖታዊ መነቃቃትን ፈጥረዋል።
ሃይማኖታዊ መነቃቃት በባሕሪው በባህላዊያን (traditionalists) እና በዘመናዊያን (modernists) መካከል ፍትጊያ መፍጠሩ አይቀሬ እንደመሆኑ መጠን አማኞች በተፎካካሪ ቡድኖች ተቦዳድነው ክርክር መፍጠራቸው አልቀረም። ምንም እንኳን ድብቅ ፍጥጫዎች (isolated confrontations) መጀመሪያ አካባቢ ይታዩ የነበረ ቢሆንም በአስገራሚ ሁኔታ በጊዜ ሂደት የባህላዊያኑም ሆነ ዘመናውያኑ ንቃተ ሕሊና ማደግና የተሻሉ የመዳረሻ ሥልቶችን መጠቀም መነቃቃቱ ሰላማዊ ግስጋሴ እንዲኖረው አድርጓል።
ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ለውጥን እና የሃይማኖት መነቃቃትን በተመሳሳይና በአንድ ወቅት ማስተናገዱ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ንቃት ከፍ እንዲል በማድረጉ ምክንያት አንዳንድ ወገኖች ሁለቱ የተለያዩና ለየብቻ የተከሰቱ ለውጦች አንድ ክስተት መስለው እንዲታዩዋቸው ሆኗል። በዚህም ‹‹አክራሪነት›› በሚል ፈርጀውታል።
1. 3. ባለበትየሚረግጠውመንግሥት
በሙስሊሙ ማኅበረሰብ መካከል ከላይ የጠቀስናቸው ለውጦች ተካሄደው ሳለ መንግሥት ለውጡን ለማስተናገድ ያደረገው መዋቅራዊ ማስተካከያ አለመኖሩ ሌላው ችግር ነው።
ሀ/ ማዕከላዊው አሥተዳደር በፌዴራሊዝም በመተካቱ ዱሮ ተገፍተው የነበሩ ቡድኖች ልሂቃን (elites) ከገዢው ፓርቲ ጋር በሚኖር ትሥሥር ሥር ከአገሪቱ ሐብት ተካፋይ እንዲሆኑና ሕዝባቸውንም እንዲያስተዳድሩ አድርጓል። ነገር ግን ያገኙት የይስሙላ ሥልጣን ከክልላዊ፣ ዞናዊና አውራጃዊ ደረጃ ያለፈ ባለመሆኑ ወደ ላይ በመሰላሉ የመውጣት ዕድል (upward mobility) አላገኙም። በሚኒስትር ደረጃ ጥቂት ሙስሊሞች ከመኖራቸው ባለፈ ማዕከላዊው አሥተዳደር እና ፖለቲካዊ መዋቅር ውስጥ ሙስሊሞች የሉም። በመሆኑም የታችኛው መንግሥታዊ መዋቅር ውስጥ የሙስሊሞች ብቅ ማለት የፈጠራቸው ማኅበረሰባዊ ለውጦች ቢኖሩም የላይኛው ማዕከላዊ መዋቅር ከነዚህ ለውጦች የተጋረደ ነው። ለውጡን ለማስተናገድ ያመቻቸው ነገርም የለም።
ለ/ የአገራዊ ማንነት (identity) ቅርፅ አሁንም አለመቀየሩ ሙስሊሙ በገዛ አገሩ የባዕድነት ስሜት እንዲሰማው ካደረጉ እንቅፋቶች አንዱ ነው። የይስሙላ እኩልነት እና የተሻለ ሃይማኖታዊ ማኅበረሰቦችን የማስተናገድ ሁኔታ ከመንግሥት በኩል ቢኖርም የኢትዮጵያ ማንነት፣ ተምሳሌትና ይዘቱ ጭምር (symbol and compostion) አሁንም ከክርስትና ጋር የተዛመደ ነው። ለማሳያነት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችን እና ኤምባሲዎችን መጎብኘት ብቻውን በቂ ነው። ይህ ዓይነቱ ውሱን አገራዊ ማንነት ደግሞ አዲሱን ሙስሊም ትውልድ የማስገለል ሚና ይጫወታል።
እነዚህ የተማረ፣ ጉጉ እና ማንነቱን የቀረፀ ትውልድ ፍሬ የሆኑ ወጣቶች ደግሞ ከላይ የተጠቀሱት ሁኔታዎች የተገፉ እንዲመስላቸው ያደርጋሉ። ‹‹ተገፋን›› ብለው ገለል ይላሉ። ነገር ግን እንደ አባቶቻቸው ኑሯቸውን የሚገነቡበት ሌላ ሞያ ስለሌላቸው ተመልሰው በሩን መቆርቆርና ተጨባጩን ለመለወጥ መታገል ይጀምራሉ። አሁን እየሆነ ያለውም ይኸው ነው።
1. 4. አባባሽየመንግሥትፖሊሲዎች
ሀ/ አሁን በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ሥልጣኑን ሲቆጣጠር ዋነኛ ሥጋቱ የነበረው የኦሮሞ ብሔርተኝነት ነበር። የኦሮሞ ብሔርተኝነት ደግሞ ከጅማሮው አንሥቶ የሃይማኖት መሪዎችን የማካተት፣ የማበረታታትና ከነሱ ድጋፍ የማግኘት ሁኔታ ነበረው፤ በተለይ ደግሞ ከሙስሊም እና ፕሮቴስታንት የሃይማኖት መሪዎች በኩል። አገዛዙ ይህንን የሙስሊሞች ድጋፍ ከእንጭጩ ለማክሰም በባሕላውያኑ እና በዘመናውያኑ ሙስሊሞች መካከል ከዱሮም የነበረውን ልዩነት በሚገባ ተጠቅሞበታል። ይህ በመንግሥት ጣልቃ ገብነት የተራገበው ልዩነት አሁን ለተፈጠረው ንቅናቄ አንዱ ምክንያት ነው።
ለ/ መንግሥት ልክ እንደ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን ሁሉ እስላማዊ ተቋማትንም በራሱ ቁጥጥር ሥር በማዋል ለራሱ ፖለቲካዊ ጥቅም አውሏቸዋል። በውጤቱም አንዳንድ የሃይማኖት መሪዎች እንደ መንግሥት አስፈጻሚ ባሕሪ ሲላበሱ፣ ተቋማቸውም ልክ እንደ መንግሥት ተቀፅላ መዋቅር መሆን ጀመረ። ይሄኔ አማኞች በተቋማቱ ላይ ያላቸው እምነት በመሳሳቱ ኢ-መደበኛ አመራርና ድርጅቶች ብቅ ማለት ጀመሩ።
ሐ/ ባለፉት አሥር ዓመታት የመንግሥት አሰላለፍ ወደ ቀን ዘመምነት ተቀይሯል። በዓም አቀፍ ደረጃ የተከሰቱ ለውጦች የፈጠሩትን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታና ለሥልጣኑ አስጊ የሆኑ ውስጣዊ ክስተቶችን ተከትሎም ቀደም ሲል ማርክሳዊ የነበረው መንግሥት የቀኝ ዘመም ፖለቲካ አሰላለፍን መርጧል።
በሂደት አላስፈላጊ ክልከላዎችን (ትምህርት ቤት ውስጥ ሂጃብና ሶላትን መከልከልን የመሰለ) በማስተዋወቅ፣ ረዘም ያለ ፂም ያላቸውን ወጣቶች በማዋከብና በአንዳንድ የመንግሥት ባለሥልጣናት ቅያሜ የሚፈጥሩ ንግሮችን በማስነገር ስትራቴጂውን ገፋበት። ይህ ደግሞ በተራው የድሮው ጭቆና ቁስል እንዲያመረቅዝ በማድረጉ ከፍተኛ መነቃቃት በሙስሊሙ ዘንድ ተፈጠረ። መንግሥት ሙስሊም የመብት ንቅናቄ አራማጆችን ‹‹የኅቡእ ታጣቂ ቡድን አባል ናቸው›› በሚል ማዋከቡና ከውጭ እንዲመጣ የተደረገው የሃይማኖት አንጃ ከፍተኛ ተቃውሞ ሲገጥመው ‹‹አለም አቀፍ አሸባሪዎች የመደቡት በጀት ሥራ ነው›› በሚል አጀንዳ ሊያስቀይር መሞከሩ ጥሩ አይደለም፤ ለዘብተኞች እንዲዳከሙና ጠንከር ያለ አቋም ያላቸው ደግሞ ኃይል እንዲያገኙ ያደርጋልና።
በተመሣሣይ ሁኔታ የቀኝ ዘመም ፖለቲካዊ አሰላለፍ በ 1997 ምርጫ ወቅት ዳግም በማንሠራራቱ ገዢው ፓርቲ እንደአፀፋ የኢትዮጵያ ብሔርተኝነትን (Ethiopian Nationalism) ከፍ ባለ ድምጽ መዘመሩ እንደሚያዋጣው በመገመት ተያይዞታል። በሚሌኒየሙ ጅማሮ የተጀመረው የ‹‹ኅዳሴ›› ፕሮፓጋንዳ ወደ አባይ ግድብና ተያያዥ ሥጋቶቹ ተሸጋግሯል። በመሆኑም አዲሲቷ ኢትዮጵያን የመገንባቱ መፈክር ተቀይሮ ‹‹የዱሮ ታላቅነታችንን መመለስ›› በሚል ተተክቷል። ያለፈው ታሪካችን ደግሞ ለሙስሊሙ ማኅበረሰብና ለሌሎች ጭቁኖች ሁሉ የነበረው ትርጉም የማያስደስት በመሆኑ አሁን መንግሥት እያስተላለፈ ያለው መልዕክት ከዱሮው ያልተለየ ይሆንባቸዋል። እናም ይህ ሕዝበ ሙስሊሙን እንደ ውጭ አካል የማየትና ጥያቄውን የመኮነን አቅጣጫ የመገለል ስሜቱን እንደ አዲስ በመቀስቀስ ንቅናቄ ፈጥሯል።
የፖለቲካ አመራርክፍተትና ምሁራዊ ምሪት አልባነት
የሙስሊሙም ሆነ ክርስትያኑ ማኅበረሰብ ሃይማኖታዊ መነቃቃት እየጦዘ ያለው በፖለቲካ መሪዎችና በምሁራን ዘንድ ጠንካራ ውይይት (discourse) በጉዳዩ ዙሪያ በሌለበት መሆኑ ችግሩን አባብሶታል። ሃይማኖት ፖለቲካውን ሠርጎ እንዳይገባ (politicization of religion) በሚደረገው ጥንቃቄም የፖለቲካ መሪዎች ወደ ችላ ባይነት ወይም ለሃይማኖታዊ ውይይት ስሱ (sensitive) ወደ መሆን አዘነበሉ። በውጤቱም ፖለቲከኞችና ምሁራን በሃይማኖት ዙሪያ፣ በተለይ ደግሞ እስልምናን በተመለከተ ጥናት ማጥናትም ሆነ አስተያየት መስጠትን እንደ አደገኛ ጨዋታ ቆጠሩት። ይህ ፍርሃት ከመስከረም አንዱ ጥቃት በኋላም ጨምሮ ታይቷል። ሙስሊም ፖለቲከኞችም አጀንዳውን ስለሚፈሩት ከማኅበረሰባቸው እንዲነጠሉ ሆነዋል። ጥቂት ሙስሊም ምሁራን ናቸው ደፍረው ስለ እስልምና የሚከታተሉት፣ የሚያጠኑትና በማኅበረ-ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚጽፉት።
አንዳንዶች በኢሕአዴግ ከፍተኛ የሥልጣን መዋቅሮች ውስጥ የሚገኙ ጥቂት ሙስሊም ባለሥልጣናትን በማየት ተሳትፎው ጥሩ እንደሆነ ሊሞግቱ ይሞክራሉ። ነገር ግን እኒህን ባልሥልጣናት ሙስሊሙ እንደ ሙስሊም መሪዎች አልተቀበላቸውም። ምክንያቱም ከማኅበረሰባቸው ጋር ያላቸው ትስስር የሳሳ፣ የማኅበረሰባቸውን አመለካከትም ሆነ ፍላጎት የማይረዱ፣ ግድ የማይሰጣቸውም ጭምር ስለሆኑ ነው። እንዲህ ስል ባለሥልጣናቱ ሃይማኖትን የወገን አሠራር ይከተሉ ማለቴ አይደለም። እኔ እያልኩ ያለሁት ማኅበረሰባቸው ውስጥ ሥር የተከሉ ቢሆኑ ኖሮ ለመንግሥት ትክክለኛ መረጃ ባደረሱና የመንግሥትንም ፖሊሲዎች የበለጠ ወደ ሕዝቡ ማስረፅ በቻሉ ነበር ነው።
ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዘንድም ቢሆን ተመሳሳይ ነገር ነው ያለው። ሁሉንም ሃይማኖቶች ባማከለ መልኩ የሚንቀሳቀሱት ብሔርተኞች (nationalists) ሲቀሩ ሌሎቹ በሙሉ ያላቸው የሙስሊም ተሳትፎ ወደ ዜሮ የተጠጋ ነው። በቀደመው ጊዜ ውስጣዊ ትስስራቸውን ጠብቆ ለማቆየት፣ ከመስከረም አንዱ ጥቃት በኋላ ደግሞ በሽብርተኝነት ላለመፈረጅ ሲሉ እስልምናን መሸሽ ይመርጣሉ። ይህ በአመራሮቻቸው መካከል የሙስሊሞች መታጣት የሙስሊሙን ማኅበረሰብ ሮሮ፣ ፍላጎት፣ አመለካከትና ስሜት እንዳያውቁ አድርጓቸዋል። ትርክታቸውም የሙስሊሙን ድጋፍ እና ተሳትፎ የሚገፋ እንጂ የሚያቀርብ አይደለም።
የፖለቲካ ልሂቃን ድርጅቶቻቸው የአንዱን የሃይማኖት ማኅበረሰብ ብሶት፣ ፍላጎት፣ አመለካከት ካላወቁ ደግሞ ቀውስ ሲፈጠር ሊያረጋጋ የሚችል ፖሊሲ መቅረፅ ይሳናቸዋል። ይሄኔ ክፍተቱን ለመሙላት ብቅ የሚሉት እንደ ፖለቲካዊም ሃይማኖታዊም መሪ ሆነው የሚያገለግሉ የሃይማኖት መብት ንቅናቄ አራማጆች ናቸው። ይህ ደግሞ ብዝኀ ሃይማኖት ባለበት አገር ውስጥ ዓለማዊ ፖለቲካ ላይ የሚያሳድረው አሉታዊ ተፅእኖ ቀላል አይደለም::
ይኸው አመክንዮ ለልሂቃኑ መደብም ይሠራል። እስካሁን በአገራችን ኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላይ የተደረገው ጥናት እጅግ የሳሳ ነው። ባለፉት መቶ አመታት ውስጥ በጉዳዩ ላይ የተጻፉት ደህና የሚባሉ መጽሐፍት ሁለት ብቻ መሆናቸው ያስገርማል። ጄ.ኤስ ትሪሚንግሃም “Islam in Ethiopia” የሚለውን መጽሐፉን ካሳተመ ከግማሽ ምዕተ ዓመት በኋላ ነው የፕሮፌሰር ሑሴን አሕመድ “Islam in the 19th Century Wollo” የተከተለው። ከዚህ ውጭ ያሉት ሥራዎች ትናንሽ መጽሐፍቶች፣ መጣጥፎችና ምዕራፎች ናቸው። ይህ እንግዲህ ከላይ እንደጠቀስኩት አገሪቱ ማምረት የቻለችው ሙስሊም ምሁራን እጅግ ጥቂት በመሆናቸው ነው። እኒህም ጥቂቶቹ ቢሆኑ በ 2009 ካረፈው ፕሮፌሰር ሑሴን አሕመድ ውጭ በሙስሊሙ ማኅበረሰብ አኗኗር ዙሪያ ጥሩ የጽሑፍ ሥራ ያበረከቱ አይደሉም።
ምንም እንኳ የትምህርት ዕድሉ እየሰፋ የሄደ ቢሆንም እየተበራከቱ ያሉት ምሁራን ወይ ሥነ-መለኮታዊውን ክፍል ብቻ መዳሰስ፣ አልያም ከነጭራሹ ርእሱን መተው መርጠዋል። በመሆኑም ምሁራዊ ምልከታ በሌለበት ሁኔታ እውቀት እየተመረተ እና እየተሠራጨ ያለው ስሜት በተጫናቸው የንቅናቄ አራማጆች ነው። ከአስተማሪ ይልቅ አነሳሽ የሆኑ ጽሑፎች እየተበተኑ ያሉትም ለዚህ ነው። ሙስሊምም ሆነ ሙስሊም ያልሆኑ ምሁራን ጥልቅ ጥናቶችን በመሥራት ማኅበረሰቡን ማወያየትና ማሳተፍ ያለባቸውም ለዚህ ነው። ችላ ባይነቱ ከቀጠለ ግን አስከፊ ፍፃሜ ሊይዝ ይችላል።
ያልተገራጣልቃገብነት
የሙስሊሙን ኅብረተሰብ ማኅበራዊ ለውጥ ማስተናገድ ያልቻለው፣ መቻቻልን ያጠናክሩ የነበሩ ዕድሜ ጠገብ እስላማዊ ተቋማትን ቅርብ አሳቢ (short-sighted) በሆነ እርምጃ ያዳከመው፣ ሙስሊሙን ኅብረተሰብ ለማስቀየም የበቁ አጓጉል ሃይማኖታዊ ክልከላዎችን የተገበረው የኢሕአዴግ መንግሥት አሁን ደግሞ ‹‹እስልምናን ለማለዘብ›› በሚል ምክንያት አደገኛ ስትራቴጂ እየተከተለ ነው። እርግጥ ለዘብተኛነት (ሚዛናዊነት) ለአንድ አገር አስፈላጊ ግብዓት ነው። ነገር ግን ከውስጥ ከሃይማኖቱ የሚመነጭ እንጂ ከውጭ መጥቶ የሚጫን አይደለም። መንግሥት ግን ከውጭ አገር አንድን የሃይማኖት አንጃ በማስመጣት ‹‹ለኢማሞች ስለለዘብተኝነት ትምህርት እየሰጠሁ ነው›› እያለ ነው።
ይህ ስትራቴጂ በውስጡ ብዙ ችግሮች አሉት። በመጀመሪያ ደረጃ መንግሥት አንድን የሃይማኖት አንጃ መርጦ የማምጣትም ሆነ የመጫን መብት የለውም። ይህ ግልፅ ባለ ሁኔታ ከመንግሥትና ሃይማኖት መለያየት መርህ ጋር ክፉኛ የሚጣረስ ነው። በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ከላይ ከአመራር ወደታች ወደ ሕዝቡ ሃይማኖትን አውርዶ ለማጥመቅ የሚደረግ ሙከራ ሊሳካ የማይችል ስትራቴጂ ነው። የትኛውም ማኅበረሰብ ቢሆን ከውጭ የሚመጣ ተፅእኖን በጥሩ ዐይን ሊያይ አይችልም። ሃይማኖታዊ ማኅበረሰብ ሲሆን ደግሞ ጥርጣሬው የበለጠ ነው የሚጨምረው፤ ራሱን በብርቱ ለመከላከል ይሞክራልና። ስለዚህ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ መንግሥት እየወሰደ ያለውን አንድን አንጃ የመደገፍ እርምጃ ‹‹በግድ ሃይማኖትን እንደ ማስቀየር›› አድርጎ ማየቱ አስገራሚ አይደለም። በሦስተኛ ደረጃ ደግሞ መንግሥት ስትራቴጂውን የመሠረተው በተሳሳተ ሐሳብ ላይ መሆኑ ሌላ ችግር ነው። የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያንን ከፍተኛ አመራር መቀየርና መሾም ስለቻለ እስልምና ጉዳዮችም ላይ ተመሳሳይ ነገር ማድረግ እንደሚቻል አድርጎ አስቧል።
ክርስትና (በተለይ ደግሞ ኦርቶዶክስና ካቶሊክ) በምእመናን ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ያለውና ግልፅ የሥልጣን ተዋረድ መዋቅር የሚከተል የተማከለ የሃይማኖት አመራር ያላቸው ቢሆንም በእስልምናው ግን ከዚህ በተለየ መልኩ እያንዳንዱ መስጊድ እና የሃይማኖት መሪ የየራሱን ሥልጣን በነጻነት የሚጠቀምበት ሁኔታ ነው ያለው። መስጊዶችን የሚገነባው የየአካባቢው ማኅበረሰብ እንደመሆኑ መጠን ኢማሞቹም ብዙ ጊዜ ያለደመወዝ የሚያገለግሉት እዚያው ከማኅበረሰባቸው መሐል ከተመረጡ በኋላ ነው። ሰባኪያኑ (የመስጊዱ ኢማም ሊሆኑም ላይሆኑም ይችላሉ) ምእመናንን የሚስቡት በግላዊ እውቅና ሲሆን ማዕከላቶቻቸውም በዚያው ማኅበረሰብ ድጋፍ የሚቆሙ ናቸው። በመስጊዶች መካከል የተዘረጋ ኔትወርክ ባለመኖሩም አንድ ሰባኪ (ዳዒ) የሚያስተምረውን፣ አንድ ኢማም የሚሰብከውን እና መስጊዱ እንዴት መተዳደር እንደለበት የሚቆጣጠር አካል ከላይም ከታችም የለም። ይህ የተማከለ አመራር እና አገልግሎት ለመስጠት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ጉባዔ ከተቋቋመ በኋላም እንኳ ሊቀየር ያልቻለ የኢትዮጵያ እስልምና ባሕሪ ነው። ምንም እንኳ ዘመናዊው የመነቃቃት እንቅስቃሴ መደበኛ ማሠልጠኛ ማዕከላትንና ጥራቱን የጠበቀ ይዘትና የአማማር ዘይቤ ያስተዋወቀ ቢሆንም የተማከለና የተናበበ የአመራር ማዕከል ማቋቋም አልተሳካለትም። ምክንያቱም በየቦታው ያሉት መስጊዶች የየራሳቸውን ነጻነት ለማስጠበቅ ስለማይሰንፉ ነው።
በጥቅሉ የኢትዮጵያ እስላማዊ ተቋማት አደረጃጀት እጅግ ያልተማከለና ሁሉም በየራሳቸው የሚቆሙበት ስለሆነ ከላይኛው ተዋረድ የሚመጣ ለውጥ መሬት ሊያገኝ አይችልም። ለዚህም ነው ባህላዊውና ዘመናዊው ንቅናቄ ያደረጓቸው ፍትጊያዎች ከማዕከላዊው ተቋም ይልቅ መስጊዶችን በመቆጣጠር ላይ አትኩረው የቆዩት። መንግሥት ስትራቴጂውን ሲነድፍ ይንን መሠረታዊ ባሕሪ ክፉኛ በመሳቱ ልፋቱ ሁሉ መና እየቀረበት ይገኛል።
አሳስቶ ከማቅረብ ወደ ማመቻመች (From Mispresentation to Accomodation)
እስልምናና ሙስሊሙ ማኅበረሰብ በአገራችን ኢትዮጵያ ወሳኝ በሆኑ ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊና መንፈሳዊ ለውጦች ውስጥ እያለፈ ነው። ይህን መሰሉ ለውጥ ደግሞ ማኅበራዊ ውጥረት (stress) መፍጠሩ አይቀሬ ነው። ይህንን ከዓለም አቀፉ አየር ጋር አዋድደን ስናገናዝበው ውጥረቱ አጉል ትኩረትና የመረበሽ ስሜትን በውጫዊም ሆነ ውስጣዊ ባለድርሻ አካላት ዘንድ ሊፈጥር ይችላል፤ መፍጠሩም የሚጠበቅ ነው። ነገር ግን ለችግሩ አጫጭርና ጊዜያዊ የመፍትሄ እርምጃዎችን በችኮላ ከመውሰድ ይልቅ ሩቅ አሳቢ፣ አዎንታዊና አስተናጋጅ (አመቻማች) መሆኑ አዛላቂ ሆኖ ይገኛል። ለዚህ ደግሞ የሚያስፈልገው ስለኢትዮጵያ ሙስሊም ማኅበረሰብ ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊና መንፈሳዊ እውነታ ትክክለኛና የጠለቀ እውቀት መጨበጥ ነው።
የመንግሥት ባልሥልጣት እየተፈጠረ ያለውን የሙስሊሞች የንቅናቄ ስሜት አንሻፈው ማቅረባቸውን ማቆም ይገባቸዋል። በዚህ መጣጥፌ ውስጥ ለማሳየት እንደሞከርኩት እስላማዊ መነቃቃቱ የዓለማቀፍ ክስተቶች ተፅእኖ ያረፈበትና የክስተቶቹ አንድ አካል ጭምር ቢሆንም ተዋናዮቹ፣ መግፍዔው (motive) እና መንስዔዎቹ አገር በቀል ናቸው። በቅርቡ በዶክተር ቴሪ (ተርጂ) ኦስቴቦ የተሠራው “Religious Change among Oromo Muslims in Bale” የተሰኘ ጥናት እንደሚያሳየው አሥርት ዓመታትን የፈጀው ዘመናዊው የዳግም መነሳሳት (revivalism) ንቅናቄ የተነሣው፣ የተቀረፀውም ሆነ በቁጥጥር ሥር የዋለው በአገር በቀል ተጨባጮች ነው። ይህ የትኛውም ሚዛናዊና ከወገንተኝነት የፀዳ አእምሮ ያለማመንታት የሚቀበለው እውነታ ነው።
በተመሳሳይ ሁኔታ ምንም እንኳን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በመንፈሳዊ ጉዳዮች ከሌሎች አገራት ሙስሊሞች ጋር አንድነት እና አጋርነት ቢኖራቸውም ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ብሶቶቻቸውን ያቅጣጩት ወደ ኢትዮጵያው መንግሥት ነው። እኒህን እውነታዎች ለጊዜያዊ ጥቅም ሲባል አንሻፍፎ ማቅረብ ለውጡን ለማስተናገድ የማይመች ከባቢ ከመፍጠሩም ሌላ ውጥረቱንም የበለጠ ያጎነዋል። በቀደሙት ዘመናት የሙስሊሞች ጥያቄ ሃይማኖታዊ ነጻነትና እኩልነትን በመጠየቅ የተወሰነ ነበር። ዛሬ ግን አዲሱ ሙስሊም ትውልድ መካተትን፣ ውክልናን እና ሙሉ ተሳትፎን ነው እየጠየቀ ያለው፤ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት ላይ ከተነሣው አገራዊ ተቃውሞ ሌላ ማለት ነው።
በጥቅሉ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ፍላጎቶቻቸው፣ ዕይታዎቻቸው እና ምኞቶቻቸው ሁሉ በፖሊሲ ቀረፃ፣ በአገራዊ ትርክትም ሆነ ምስል ቀረፃ ውስጥ እንዲካተቱላቸው እየፈለጉም፣ እየታገሉም ነው። እኒህ ደግሞ የሃይማኖታዊ እንቅስቃሴ ጥያቄዎች አይደሉም፤ በሰላማዊ ተቃውሞ ላይ የተመሠረተ ዓለማዊ እና ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ እንጂ። ይህ በአገሪቱ ድንበሮች ሥር ተወስኖ ያለ የመብት እንቅስቃሴ ጥያቄውን ያቀረበው ለመንግሥት እንደመሆኑ መጠን መፍትሄውንም የሚጠብቀው ከዚያው ነው።
የሥርዓቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እያሰሙት ያለው የሥጋት ጩኸት እና ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ አካላት ጠጣር ገለጻ እየጮኸ ቢሆንም ድሮም ሆነ ዛሬ የተለየ ኢስላማዊ የፖለቲካ ሰውነት እንዲኖር ሙስሊሞች የጠየቁበት ጊዜ የለም። መሰል አቀራረብን የመረጡ ፖለቲካዊ ተቋማት እንኳ ከሙስሊሙ ኅብረተሰብ ክፉኛ ተቃውሞ ገጥሟቸው ከፊሎቹ አስተሳሰባቸውን ለመለወጥ ሲገደዱ ከፊሎቹ ከስመዋል።
እስካሁን ድረስ ከልላዊ እና አገራዊ ታጣቂ ቡድኖች ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያደርጉለትም፣ መንግሥትም ተንኳሽ እርምጃዎችን ቢወስድበትም የሙስሊሞች ንቅናቄ የኃይል መጠቀምን ዝንባሌ አላሳየም። ይህ ለኔ የሚያሳየኝ እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ነጻነት፣ የሕግ የበላይነት እና እኩልነት ከሕግነት ባለፈ ያለ ሃይማኖት ልዩነት ለሁሉም ኢትዮጵያውያን እውን የሚሆኑበትን ተጨባጭ ከመፈለግ የመነጨ ትግል እንደሆነ ነው። እያደገ ያለው የሙስሊሞች ንቅናቄ መድልዎን፣ ችላ ባይነትን እና ጣልቃ ገብነትን እየተቃወመ ያለ በመሆኑ የተበታተነው ዴሞክራሲን የማስፈን ትግል አካል ነው ማለት ነው። የሥጋት ደውል የሚያሰሙትን ጥቂት ጩኸቶች ወደጎን በመግፋት ጥያቄዎቹን ወደ መመለስ ማተኮሩ ኢትዮጵያን ወደ መረጋጋት እና አሳታፊ ልማት የሚያሻግር እጅግ አስፈላጊ እርምጃ ነው።
(አቶ ጃዋር ሙሐመድ በእውቁ የአሜሪካ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪ ናቸው። በአገር አቀፋዊ እና ዓለም አቀፋዊ ፖለቲካዊ ክስተቶች ዙሪያ ጥልቅ ፖለቲካዊ ትንታኔ በመስጠት ይታወቃሉ። ከላይ የቀረበው ጽሑፋቸውም ወቅታዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ጉዳይ አስመልክቶ ያቀረቡት ነው።
ለጽሑፋቸው ማጠናከሪያነት አሥር ያህል መጽሐፍቶችንና የጥናት ወረቀቶችን በዋቢነት ጠቅሰዋል።)

ኢስላም - የዓለማችን ታላቁ ሥልጣኔ

አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ እንዲህ አለ
وَكَذَٰلِكَ جَعَلْنَاكُمْ أُمَّةً وَسَطًا لِّتَكُونُوا شُهَدَاءَ عَلَى النَّاسِ وَيَكُونَ الرَّسُولُ عَلَيْكُمْ شَهِيدًا [٢:١٤٣]
“እንደዚሁም ( እንደመራናችሁ) በሰዎች ላይ መስካሪዎች ልትሆኑና መልእክተኛውም በናንተ ላይ መስካሪ ይሆን ዘንድ ሚዛናዊ ህዝቦች አደረግናችሁ።” (ቁርኣን 2፡143)
የኢስላማዊ ሥልጣኔ ዋና ዋና ባህሪያት
ኢስላም የዓለማችን ሃይማኖት እንዲሆንና አንዱን ጫፍ ከሌላኛው የዓለማችን ጫፍ የሚያገናኝ ታላቅ ሥልጣኔን ይፈጥር ዘንድ ነው ትልቁ ዓላማው። በመሆኑም ገና በመጀመሪያዎቹ የሙስሊም ከሊፋዎች (የነቢዩ ተተኪዎች) ዘመን መጀመሪያ ዐረቦች ቀጥሎም ፐርሺያዎች ኋላ ላይ ደግሞ ቱርኮች ድንቅ የሆነ ኢስላማዊ ሥልጣኔ ለማስቀመጥ ተንቀሣቅሰዋል። በ13ኛው ክፍለዘመን ደግሞ አፍሪካና ህንድ ትልቅ የኢስላማዊ ሥልጣኔ ማዕከል ለመሆን የበቁ ሲሆን ብዙም ሣይቆይ ደግሞ ኢስላማዊ መንግስታት በማሌዤያና ኢንዲኔዠያ አካባቢ ሊመሠረቱ ችለዋል። የቻይና ሙስሊሞችም እንዲሁ በመላዋ ቻይና ተበትነው የእስልምናን ስልጣኔ አስተዋውቀዋል።
ኢስላም የጎሣ መደቡ አሊያም ዘሩ ከየትኛውም ወገን ይሁን የሁሉም የዓለም ህዝቦች ሁሉ ሃይማኖት ነው። ለዚህም ነው ኢስላማዊ ሥልጣኔ ዘረኝነትን ወይንም የጎሣ ልዩነትን በሚፃረር መልኩ ፍጹም አንድነት ላይ መሠረቱን ያደረገው። እነኚህ ዋና ዋና የሚባሉ የዘርና የጎሣ መደቦች ከዐረብ፣ ከፐርሺያ (ኢራንና ከፊል ኢራቅ)፣ ከቱርክ፣ ከአፍሪካ፣ ከህንድ፣ ከቻይና እና ከማሌዠያ እንዲሁም ከሌሎች እስልምናን ከተቀበሉና ኢስላማዊ ሥልጣኔን ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ካደረጉ ትናንሽ የጎሣ ክፍሎች ሊሆን ይችላል። በሌላ በኩል ኢስላም ከሌሎች ቀደምት ሥልጣኔዎች እውቀታቸውን፣ ሣይንሣቸውን፣ ትምህርታቸውን፣ ባህላቸውንና ሌሎች ጠቃሚ ነገሮችን ወደራሱ ዓለም አመለካከት ማስገባትን አይቃወምም። አመለካከቶቹ የኢስላምን መሠረታዊ ህግጋት እስካልተፃረሩ ድረስ። እያንዳንዱ ኢስላምን የተቀበለ ጎሣ ወይንም ብሄር ለዚያ ለሚገኝበት ኢስላማዊ ሥልጣኔ የራሱ አስተዋጽኦ አለው። ከሁሉም በላይ ደግሞ ኢስላማዊ ወንድማማችነትና የእህትማማችነት ፅንሰ ሀሣብ በአንድ ጎሣ፣ ዘር፣ ቋንቋና አካባቢ ከመተሣሠር በባለፈ ትልቅ ትርጉም አለው። እነኚህ ሁሉ ነገሮች ዓለማቀፍ የሆነው የኢስላማዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት አካል ናቸውና።
በኢስላም የተፈጠረው ዓለማቀፋዊ ሥልጣኔ የሰው ልጆች በጎሣና በዘር ቢለያዩም የተለያዩ ጥበቦችንና እውቀቶችን አብረው እንዲሠሩና እንዲያመርቱ ያበረታታል። ምንም እንኳ ለሥልጣኔው መጎልበት ትልቁ ድርሻ የእስልምናና የሙስሊሞች ቢሆንም ሙስሊም ያልሆኑ ማህበረሰቦች በተለይም “የመጽሃፉ ባልተቤቶች (አይሁዶችና ክርስቲያኖች)” ፍሬው ለያንዳንዱ ሰው በደረሰው ምሁራዊ እንቅስቃሴ ላይ የነቃ ተሣትፎ ነበራቸው። ዛሬ በአሜሪካ የሚታየው ሣይንሣዊ ድባብ ቀደም ባለው ጊዜ ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ ሣይንቲስት ወንድና ሴቶች አንድ ላይ በሚማሩበት ወቅት እያንዳንዳቸው ለእውቀት ማደግ ጉልህ ተሣትፎ ያደረጉበትን ጊዜ ያስታውሰናል።
የኢስላም ምንጭ የሆነው ዓላማቀፉ ሥልጣኔ ወደክልሉ የገቡትን ሰዎች አዕምሮ በማነቃቃትና ለምርምር በመጋበዝ ረገድም እጅግ የተሣካ ሥራ ሠርቷል ማለት ይቻላል። ይህም በመሆኑ በአንድ ወቅት ዘላን የነበሩ ዐረቦች የሳይንሱንና የእውቀቱን ዓለም እስከመምራት የደረሱበት ሁኔታ ነበር። ከእስልምና በፊት ትልቅ ሥልጣኔ የነበራቸው ፐርሺያኖች በእስልምና ዘመን በበለጠ መልኩ የሣይንስ እውቀትን ለዓለም አበርክተዋል። ስለ ቱርኮችም ሆነ ስለ ሌሎች እስልምናን የተቀበሉ ክፍሎች ይህንኑ ማለት ይቻላል። የእስልምና ሃይማኖት የተለያዩ ጎሣና መደብ የሆኑ የሰው ልጆች የተሣተፉበትን ዓለማቀፋዊውን ሥልጣኔ በመፍጠሩ ብቻ ሣይሆን እውቀትንና ባህላዊ ህይወትን ከዚህ በፊት ባልታየ መልኩ በማሣደጉ በኩልም ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ለ800 አመታት ያህል ዐረብኛ የአለማችን ዋና የትምህርትና የሳይንሣዊ ቋንቋ እውቀት ምንጭ ሆኖ ቆይቷል። የእስልምናን መሰበክ ተከትለው በመጡ የመጀመሪያዎቹ ክፍለ ዘመናት የሙስሊሙን ዓለም የተለያየ ክፍል ይገዙ ነበሩ ትናንሽ ስርወ መንግስታት ለኢስላማዊው ባህል አስተሣሰብ ማበብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ነበራቸው። በርግጥ ይህ ልምድና የዘመነ እንቅስቃሴ በያዝነው ክፍለዘመን መጀመሪያ አካባቢ በሙስሊሞች እምነት መዳከምና በውጭ ተፅእኖ የተነሣ ተዳፍኖ የነበረ ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ግን በሙስሊሙ ዓለም የተለያዩ አካባቢዎች እንደ አዲስ በማንሠራራቱ ሙስሊሞች የራሣቸው የሆነ የፖለቲካ ነጻነት እስከ መመለስ የበቁበት ሁኔታ ይታያል።
የእስልምና ታሪክ መጠነኛ ዳሠሣ
  • ኹለፋኡ ራሽዲን ( ከነቢዩ ሞት በኋላ የተተኩ ወደ ቀጥተኛው ጎዳና የሚመሩ ተተኪዎች )
የነቢዩን ሰለላሁ ዐለይህ ወሠለም ሞት ተከትሎ የነቢዩ የቅርብ ወዳጅና ከአዋቂ ወንዶች ኢስላምን ለመቀበል የመጀመሪያው የነበሩት አቡበክር ረዲየሏሁ ዐንሁ ከሊፋ ( የሣቸው ተተኪ ) ሆኑ። እርሣቸውም ለሁለት አመታት ካስተዳደሩ በኋላ ዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁ በእግራቸው ተተኩ። ዑመርም ለ10 አመታት ያህል ህዝበ ሙስሊሙን ያስተዳደሩ ሲሆን በርሣቸው ዘመን እስልምና የፐርሺያን ( የዛሬዋን ኢራንና ከፊል ዒራቅን እስከ ፓኪስታን ) ግዛት አልፎ ሶሪያና ግብፅን አጠቃሎ ከምስራቅ እስከ ምእራብ የዓለም ዳርቻዎች ሊስፋፋ ችሏል። ኢየሩሣሌም የደረሰውን የሙስሊሙን ጦር በእግር የመሩትና የክርስቲያኖች ቦታዎችና ይዞታዎች ለጥቃት እንዳይጋለጡ ያዘዙትም እርሣቸው ነበሩ። የመጀመሪያውን የህዝብ ግምጃ ቤት ለሙስሊሙ ዓለም ያስተዋወቁ ሲሆን ዘመናዊውን የፋይናንስ ሥርኣት አስተዳደር ዘርግተዋል። ከዚህም ባለፈ ለኢስላማዊው መንግስት ግብአት ሆነው ለሚያገለግሉ በርካታ ወሣኝ ነገሮች መሠረት ጥለዋል።
በዑመር የተተኩት ዑስማን ረዲየሏሁ ዐንሁ ነበሩ። እርሣቸውም ለ12 አመታት ያህል ህዝበ ሙስሊሙን ያስተዳደሩ ሲሆን በርሣቸውም ዘመን ኢስላም መስፋፋቱን አላቆመም ነበር። ዑስማን የቅዱስ ቁርኣንን ዋና ቅጂ ወደ አራቱም የዓለም ማእዘናት በመላክም ይታወቀሉ። እርሣቸውን የተኩት አራተኛው ኸሊፋ ዓሊ ረዲየሏሁ ዐንሁ ነበሩ። ዓሊ ኢብኑ አቢጧሊብ ልብ በሚነኩ ምክሮቻቸውና መልእክቶቻቸው እንዲሁም በጀግንነታቸው ዛሬም ድረስ ይታወቃሉ። በርሣቸውም ሞት በሙስሊሙ ልብ ውስጥ ትልቅ ክብርና ቦታ የነበረው የኩለፋኡ ራሽዲን ዘመን ሊያበቃ ችሏል።
  • ኸሊፋዎች    
በ661 የተመሠረተው የኦማያድ /ኡመያውያን/ ሥርወ መንግሥት የአንድ ምእተ አመት ያህል እድሜ ነበረው። በዚህን ጊዜ ዳማስቆ ከምእራብ ቻይና እስከ ደቡባዊ ፈረንሣይ ድረስ ተንሠራፍቶ ለነበረው የሙስሊሙ ዓለም ግዛቶች ዋና ከተማ ሆና አገልግላለች። በዚህ ዘመን የሙስሊሞች ግዛት ከሰሜን አፍሪካ እስከ ስፔን ድረስ የዘለቀ ሲሆን በምእራብ በኩል እስከ ፈረንሣይ በመካከለኛው ኢስያ ደግሞ እስከ ሲንድና በምሥራቅ እስከ ትራኖክሲያና ሊስፋፋ ከመቻሉም በላይ መሠረታዊ የሆኑ ማህበራዊና ህጋዊ አገልግሎት የሚሠጡ ድርጅቶችም ሊመሠረቱ ችለዋል።
የኡመያውያኑን ዘመን መውደቅ ተከትሎ ወደ ሥልጣን የመጣው የአባሲድ (አባሳውያን) ሥርወ መንግስት ዋና መቀመጫውን ወደ ባግዳድ ያዛወረ ሲሆን ባግዳድም በዘመኑ ወደር የማይገኝላት የትምህርትና የባህል ማእከል እንዲሁም ለሰፊው ሙስሊሙ ዓለም የአስተዳደርና የፖለቲካ ልብ ሆና አገልግላለች።
አባሳውያን ለ500 አመታት ያህል ያስተዳደሩ ሲሆን ኋላ ላይ ቀስ በቀስ ሀይላቸው ተዳክሞ በቅጡ የታጠቀ ወታደራዊ ሀይል ባላቸው የተለያዩ ሱልጣኖችና ልኡላውያን ላይ ሥልጣን ያላቸው በመምሰል ለምልክት ብቻ የቀሩ መሪዎች እስከመሆን ደርሰው ነበር። በመጨረሻም የአባሲድ ሥርወ መንግስት ሁላጉ የሚባል የሞንጎላውያን መሪ በ1258 ባግዳድን ሲይዝ ከናካቴው ሊወድቅ ችሏል። በወቅቱ ሞንጎሎቹ ትልቁን ቤተመፃህፍት ጨምሮ ከተማዋን በከፍተኛ ሁኔታ አውድመው ነበር።
አባሣውያን ባግዳድን ያስተዳድሩ በነበረበት ዘመን በርካታ ጠንካራ ሥርወ መንግስታትንም የመሠረቱበት ሁኔታ ነበር። ከነዚህም ወስጥ ፋጢማውያን፣ አዩባውያን፣ እና መምሉኮች የሚባሉት በግብጽ በሶሪያና በፍልስጤም ከፍተኛ ሀይል ነበራቸው። የሙስሊሙንና የምእራቡን ዓለም ግንኙነት አስመልክቶ በዚሁ ዘመን ትልቅ ክስተት የነበረው በጳጳሱ የታወጀውና በበርካታ የአውሮፓ ነገስታት ድጋፍ ያገኘው ተከታታይ የመስቀል ጦርነት ነበር። ምንም እንኳ ምክኒያቱ ፖለቲካዊ ቢመስልም ያነጣጠረው ግን ቅዱሣን መሬቶችን በተለይ ኢየሩሣሌምን (ቁድስን) መልሶ በክርስቲያኖች እጅ ለማስገባት ነበር። በዚህም ክርሲቲያኖቹ አውሮፓውያን በመጀመሪያ አካባቢ የተወሰነ ድል ያገኙ ሲሆን የሶሪያንና የፍልስጤም ከፊል ግዛቶችን ለመቆጣጠር ችለው ነበር። በመጨረሻ ግን በታዋቂው ጀግና ሰላሃዲን አልአዩቢ በሚመራው ጦር በ1187 መስቀል ጦረኞቹን በማሸነፉ ኢየሩሣሌም እንደገና በሙስሊሞች እጅ ልትገባ ችላለች።
ከዐረብኛ የተወሠዱ አንዳንድ የእንግሊዝኛ ቃላት
እንግሊዝኛ    
ዐረብኛ
አድሚራል (ADMIRAL)
አሚረል- ረህል
አዶቤ (ADOBE)
አልቱብ
አልኬሚ (ALCHEMY)
አልኪሚያ
አልኮቭ (ALCOVE)
አልቁባ
አለምቢክ (ALEMBIC)
አለንቢቅ
አልጀብራ (ALGEBRA)
አል ጃቢር
አምበር (AMBER)         
አምበር
አሙሌት (AMULET)
ሃማኢል
አንቲሞኒ (ANTIMONY)
ኢትሚድ
አረቲቾክ (ARTICHOKE)
አልከርሹፍ
አትላስ (ATLAS)
አትላስ
አዚሙት (AZIMUTH)
አል ሱት
ባናና( BANANA)
ባናና
ባሮቅ (BAROQUE)
ቡርቃ
ኬብል (CABLE)
ሀብል
ካሜል (CAMEL)
ጀመል
ቼክሜት (CHECKMATE)
ሻህማት
ኮፊ (COFFEE)
ገህዋ
ኮተን (COTTON)
ኩትን
ጊራፌ (GIRAFFE)
ዘራፋ
ጃስሚን (JASMINE)
ያስሚን
ሌመን (LEMON)
ሌሙን
ሉት (LUTE)
አል ኡድ
መጋዚን (MAGAZINE)
መካዚን
ማስክ (MASK)
ማሰካራ
ሞንሱን (MONSOON)
መዋሲም
ሙስክ (MUSK)
ሙስክ
ናዲር (NADIR)
ናዚር
ኦሬንጅ (ORANGE)
ናራንጅ
ራይስ (RICE)
ሩዝ
ሳፋሪ (SAFARI)
ሳፋራ
ሳፈሮን (SAFFRON)
ዘዕፋራን
ሳንዳልውድ (SANDALWOOD)
ሰንደል
ሶፋ (SOFA)
ሱፋ
ሹገር (SUGAR)
ሱከር
ሺረፕ (SYRUP)
ሸራብ/ ሹርባ
ታምቡር (TAMBOUR)
ታቡራክ
ተራውባዱር (TROUBADOUR)
ተራብ
ዜሮ (ZERO)
ሲፍር
ዚረኮን (ZIRCON)
አዝረቅ

  • ሰሜን አፍሪካና ስፔን
አባሲዶች ደማስቆን ሲይዙ ከኦማያድ ሥርወ መንግስት የሆነ አንድ ልዑል ተለዋጭ የኦማያድ አገዛዝ ለመመስረት ብሎ ረጅም ጉዞ በማድረግ ከደማስቆ ወደ ስፔን ሸሽቶ ነበር። ይህም ክስተት በስፔን ወርቃማው የኢስላም ዘመን እንዲጀመር ምክኒያት ሆነ። ኮርዶቫ በዋና ከተማነት የተመረጠች ስትሆን ኋላ ላይም በህዝብ ብዛት ብቻ ሣይሆን የባህልና የዘመናዊ ትምህርት ማእከል በመሆንም ጭምር የአውሮፓ ትልቋ ከተማ እስከመሆን ደርሣ ነበር። ኡመያውያን ስፔንን ለሁለት ምእተ አመታት ያህል ያስተዳደሩ ሲሆን በመጨረሻም ተዳክመው በአካባቢ ገዠዎች ሊተኩ ችለዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በሰሜን አፍሪካ በርካታ አካባቢያዊ ሥርወ መንግስታት አንድ ላይ በመጣመር ሁለት ጠንካራ የበርበር መንግስታትን በመመሥረት አብዛኛውን የሰሜን አፍሪካ እንዲሁም በ12ኛውና በ13ኛው ክፍለዘመን ስፔንን ጨምሮ ለማዋሀድ በቅተዋል። ከነሱ በኋላም ይሀው አካባቢ እንደገና ለምሣሌ አሁንም ድረስ ሞሮኮን በሚገዛው ሸሪፊድስ እና በመሣሠሉት ትናንሽ ስርወ መንግስታት ሊመራ ችሏል። በስፔን ግን የሙስሊሙ ሀይል የበላይነት እየተዳከመ ሄዶ በመጨረሻም በ1492 በግራናዳ የተሸነፈበት ሁኔታ ነበር። በዚህም ሙስሊሞች ለ800 አመታት ያህል ስፔንን ያስተዳደሩበት ሁኔታ ፍፃሜ አግኝቷል።
  • የእስልምና ታሪክ ከሞንጎሎች ወረራ በኋላ
ሞንጎላውያን ክፉኛ በመመታታቸው ከሙስሊሙ ዓለም ምስራቅ መሬቶች በመባረር ከሲናእ በረሃ ወደ ህንድ ለአንድ መቶ አመታት ያህል ተገፍተው ቆይተው ነበር። ነገር ግን ኋላ ላይ እስልምናን በመቀበል ‹ኤልካኒድስ› በሚባል መጠሪያ ሊታወቁ ችለዋል። ቀጥሎም በቲሙሮች የተተኩ ሲሆን የልጅ ልጆቻቸውም ሰመርቀንድን ዋና ከተማቸው በማድረግ ከ1369-1500 ገዝተዋል። የቲሞሮች ድንገት መነሣት የኦቶማን አገዛዝን መደራጀትና መስፋፋት ያዘገየ ቢሆንም ኋላ ላይ ግን ኦቶማኖች በሙስሊሙ ዓለም ትልቁ የሀይል ባለቤት ሆነዋል።
ቱርኮች ከምንም በመነሣት አጠቃላይ አናቶሊያንና የተወሰነውን የአውሮፓ ክፍል የተቆጣጠሩበት ሁኔታ አስገራሚ ክስተት ነበር። በ1453 በሚገጥመው ጦርነት ሁሌም አሸናፊ የሆነው ሜህሜት ኮንስታንኖፕልን በመውረር ለቢዛንታይኖች አገዛዝ ፍፃሜ አስገኝቷል። በዚሁ ጊዜ ኦቶማኖች ብዙውን የምሥራቅ አውሮፓ ክፍልና አጠቃላይ ሊባል በሚችል መልኩ የዐረቡን ዓለም ወረው የያዙ ሲሆን በምእራብ በኩል ሞሮኮና ሞሪታኒያ ብቻ ሲቀራቸው በዐረቡ ባህረ ሰላጤ ደግሞ የመንና ሀድረሙት ብቻ ነበር በቁጥጥራቸው ሥር ያልዋለው። በአስደናቂ መሪያቸው በሱሌይማን አማካይነት የሀይል ቁንጮ ላይም በመድረስ ጦራቸው ሀንጋሪና ኦስትሪያ ድረስ ዘለቀበት ሁኔታ ነበር።
ከ17ኛው ክፍለዘመን ቀጥሎ ባሉት አመታት የምእራብ አውሮፓውያንን ሀይል ማንሠራራትና የራሺያን መጠናከር ተከትሎ የኦቶማኖች ሀይል እየተዳከመ መጣ። በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ወቅት በምእራባውያን ሀገራት እስከተሸነፉበት ጊዜ ድረስም ቱርኮች የዓለማችን ተጠቃሽ ሀይል ሆነው ቆይተዋል። ነገር ግን በ1924 ከማል በቱርክ አታቱርክ ወደ ሥልጣን በመጣበት ወቅት ለ6 ክፍለዘመናት የቆየው የኦቶማን አገዛዝ ተወገደ። ኦቶማኖች በምእራብ ግንባር በኩል ባለው ግዛታቸው ተጠምደው ሣለም በምስራቅ በኩል ፐርሺያ ውስጥ ሣፋቪድስ የሚባል አዲስ ሥርወ መንግስት በ1502 ወደ ሥልጣን መጣ። ሣፋቪዶች የራሣቸው የሆነ ጠንካራ ግዛት የመሠረቱ ሲሆን ለሁለት ምእተ አመታት ያህል በነበራቸው እድሜም በዋናነት የበርካታ ጥበቦች መፍለቂያ ሆነው ነበር። በሰማያዊ ጡብ መስጊዶቿና በማራኪ ቤቶቿ የምትታወቀው ዋና ከተማቸው እስፈሃንም እጅግ ቆንጆ ከሚባሉ ከተሞች ለመሆን ችላለች። በ1736 አፍጋኖች ባደረሱት ወረራ የሣፋዚዶች አገዛዝ ፍፃሜ ያገኘ ሲሆን አፍጋኒስታንም በመጨረሻ በ19ኛው ክፍለ ዘመን ሙሉ ነፃነቷን ልታገኝ ችላለች። በሌላ በኩል ፐርሺያ ደግሞ የመጨረሻው የምሥራቃውያን ወራሪ ናድር ሻህ መልሦ እስኪያዋህዳት ድረስ አለመረጋጋት ውስጥ የገባችበት ነበር። ናድር ከፐርሺያም አልፎ ህንድንም እስከ መውረር ደርሦ ነበር። ቢሆንም ግን እዚያ የተመሠረተው አገዛዙ አጭር እድሜ ነበረው። ኋላም የዛንድ ሥርወ መንግስት ሥልጣን ላይ የወጣ ቢሆንም ወዲያውኑ መቀመጫቸውን ቴህራን ባደረጉት ቀጃርስ በ1779 ሊወገድ ችሏል። እነሱም እስከ 1921 የገዙ ሲሆን በመጨረሻም በፓልቪሦች ተተክተዋል።
ስለ ህንድ ስናነሣ እስልምና ወደ ምስራቃዊ ኢንዱስ ወንዝ መሬቶች የደረሰው ሰላማዊ በሆነ መልኩ ነበር። ቀስ በቀስም ሙስሊሞች በ13ኛው ክፍለዘመን መባቻ ጀምሮ የፖለቲካ የበላይነት እያገኙ መጡ። ነገር ግን እስልምናና ኢስላማዊ ባህሎች በእጅጉ እየተስፋፉ በነበረበት በዚህ ዘመን አብዛኛው የህንድ ክፍል በ1526 ከቲሙሪድ ልዑሎች መካከል አንዱ በሆነው በባቡር በመወረሯ ምክኒያት መስፋፋቱ ሊገታ ችሏል። ባቡር ጠንካራ የሞጉል ግዛትን የመሠረተ ሲሆን ከግዛቲቱም አክባር፣ ጀሀንጊር እና ሻህ ጀሃን የሚባሉ ታዋቂ መሪዎች ሊፈልቁ ችለዋል። ይሀው አገዛዝ በህንድ የብሪታኒያን ሀይል ተቋቁሞ ቆይቶ በመጨረሻም በ1857 ሊወገድ ችሏል። እሩቅ ምሥራቅ በማላይ ዓለም (ማሌዠያና ኢንዶኔዠያ አካባቢ) እስልምና ከ12ኛዉ ክፍለ ዘመን ጀምሮ በሰሜን ሱማትራ የተስፋፋ ሲሆን ሙስሊም ግዛቶችም በጃቫ ፣ በሱማትራና በዋናው የማሌዠያ ክፍል ሊመሠረቱ ችለዋል። ምንም እንኳ ሰፊው የማላይ አካባቢ በቅኝ አገዛዝ ሥር የወደቀ ቢሆንም እስልምና ግን መስፋፋቱን ቀጥሎ በዚያ አካባቢ የዛሬዎቹን ኢንዶኔዠያን፣ ማሌዠያን፣ ደቡብ ፊሊፒንስን፣ ደቡብ ታይላንድን ለመሸፈን በቅቷል። ይሀው ሰላማዊ የሆነ መስፋፋቱ ዛሬም ድረስ ወደ ሩቅ ምስራቅ ደሴቶች እየተለጠጠ ነው።
አፍሪካን በተመለከተ እስልምና ወደ ምሥራቅ አፍሪካ በመጀመሪያዎቹ የኢስላም መባቻ አካባቢ የገባ ሲሆን በዳርቻዎች አካባቢ ተወስኖ ቆይቶ ሱዳንና ሶማሊያ ብቻ ቀስ በቀስ ዐረብም ሙስሊምም ሊሆኑ ችለዋል። እስልምና ወደ ምእራብ አፍሪካ ሊደርስ የቻለው ደግሞ በግመሎቻቸው ቅፍለቶች ወደ ደቡብ የሰሃራ በረሃ ይጓዙ በነበሩ የሰሜን አፍሪካ ነጋዴዎች ነው። በ14ኛው ክፍለ ዘመን በምእራብ አፍሪካ ማሊ እና ቲምቡክቱ አካባቢ ሙሰሊም ሱልጣኔቶች የነበሩ ሲሆን ሀረር ደግሞ በምሥራቅ አፍሪካ የኢስላማዊ ትምህርት ማዕከል ነበረች። ቀስ በቀስ እስልምና ወደ መሃል አህጉሩና ወደ ደቡብም ሊስፋፋ ችሏል። ይህ አካባቢ የአውሮፓን የሀይል የበላይነት በከፍተኛ ሁኔታ የተቋቋሙ የሚገርሙ ከፍተኛ አድናቆት የተቸራቸው ዝነኛ ሰዎችን ያፈራ ነበር። አፍሪካን ሙስሊም የማድረጉ ሂደት በቅኝ አገዛዙም ዘመን ያልተቋረጠ ሲሆን አሁንም ድረስ ቀጥሎ አብዛኞች ከሰሃራ በታች የሚገኙ አፍሪካውያን ረጅሙ የኢስላም ታሪክ በአንድ ወቅት በተወሰነ አካበቢ ጥሎት ያለፈውን ልማድ የሚከተሉ ሆነው እናገኛለን።  
  • በኢስላም ታሪክ አበይት ቀናት ( ሁሉም አቆጣጠር በጎርጎርሣውያን ነው)
570
የነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) ልደት
609
የመጀመሪያው የቁርኣን አንቀፅ በነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) ላይ የወረደበት
622
የነቢዩ ሙሀመድ (ሰ.ዐ.ወ) ስደት ከመካ ወደ መዲና /ሂጅራ/። በሙስሊሞች የዘመን አቆጣጠር የመጀመሪያው ቀን
632
የነቢዩ ሙሀመድ ሰለላሁ ዐለይሀ ወሠለም ሞት
632-661
የኩላፋኡ ራሽዲን ዘመን
661-750
የኦማያድ ሥርወ መንግስት
750-1258
የአባሲድ ሥርወ መንግስት
756-1031
ኡመያውያን ስፔንን የገዙበት ዘመን
909 -1171
ፋጢሚዮች
137-1300
ሴልጁቆች
1187
ሰላሃዲን ኢየሩሣሌምን የከፈተበት
1252-1517
የመምሉኮች አገዛዝ
1258
ሞንጎሎች ባግዳድን የወረሩበት
1299-1924
የኦቶማን አገዛዝ
1369-1500
ቲሙሪዶች
1453
የኮንስታንቲኖፕል መከፈት
1492
የግራናዳ መውደቅ
1502-1736
ሣፋቪዶች አገዛዝ